የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የተቀናጁ አሠራሮችን በመጠቀም በፓርኮች ላይ የሚደርስ ጉዳት መቀነስ ተችሏል

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በብሔራዊ ፓርኮችና የዱር እንስሳት መጠለያዎች እያከናወናቸው ያሉ አሠራሮች ሕገ ወጥ ድርጊቶች እንዲቀንሱ ማስቻላቸውን ገለጸ።

ባለሥልጣኑ በጀት መድቦ በቀጥታ በሥሩ የሚያስተዳድራቸው 11 ብሔራዊ ፓርኮች እና ሁለት የዱር እንስሳት መጠለያዎች መሆናቸውን አስታውቋል።


በክልሎች ሥር ለሚተዳደሩ ብሔራዊ ፓርኮችም የስልጠና፣ የቁሳቁስና መሰል ድጋፍ እንደሚያደርግ የባለሥልጣኑ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ ታምሩ መክት ለኢዜአ ተናግረዋል።

የብሔራዊ ፓርክና የዱር እንስሳት መጠለያ ጠባቂዎችን በማሰልጠን፣ ለጥበቃ የሚሆኑ ትጥቆችን በማቅረብ፣ በቂ የሰው ኃይል በማሟላት፣ ካሉበት ሆነው መረጃዎችን የሚለዋወጡበት በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራርን እንዲከተሉ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።

በየአካባቢዎቹ የሚገኙ ነዋሪዎች የኔ ነው ብለው በንቃት እንዲጠብቁ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ መከናወኑንም ጠቁመዋል።


ወጣቶች ተደራጅተው እንዲጠብቁ የማድረግ ሥራ መከናወኑን ጠቁመው፤ ባለሥልጣኑ እየሰራቸው ያሉ አሠራሮች ከሕብረተሰቡ ትብብር ጋር ተቀናጅተው ሕገ ወጥ ድርጊቶች እንዲቀንሱ ማስቻላቸውን ተናግረዋል።

ዓለም አቀፍ ወንጀል የሆነውን ሕገ ወጥ የዱር እንስሳት ውጤቶች ዝውውር ከመቆጣጠር አኳያም፤ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአነፍናፊ ውሻዎች ጭምር የቁጥጥር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በአነፍናፊ ውሻዎች ታግዞ እየተሠራ ያለው የቁጥጥር ሥራ ውጤታማ መሆኑን አንስተው፤ በዚህም በሕገ ወጥ መንገድ የሚደረግ የእንስሳት ውጤቶች ዝውውር ቀንሷል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026