🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በብሔራዊ ፓርኮችና የዱር እንስሳት መጠለያዎች እያከናወናቸው ያሉ አሠራሮች ሕገ ወጥ ድርጊቶች እንዲቀንሱ ማስቻላቸውን ገለጸ።
ባለሥልጣኑ በጀት መድቦ በቀጥታ በሥሩ የሚያስተዳድራቸው 11 ብሔራዊ ፓርኮች እና ሁለት የዱር እንስሳት መጠለያዎች መሆናቸውን አስታውቋል።

በክልሎች ሥር ለሚተዳደሩ ብሔራዊ ፓርኮችም የስልጠና፣ የቁሳቁስና መሰል ድጋፍ እንደሚያደርግ የባለሥልጣኑ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ ታምሩ መክት ለኢዜአ ተናግረዋል።
የብሔራዊ ፓርክና የዱር እንስሳት መጠለያ ጠባቂዎችን በማሰልጠን፣ ለጥበቃ የሚሆኑ ትጥቆችን በማቅረብ፣ በቂ የሰው ኃይል በማሟላት፣ ካሉበት ሆነው መረጃዎችን የሚለዋወጡበት በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራርን እንዲከተሉ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።
በየአካባቢዎቹ የሚገኙ ነዋሪዎች የኔ ነው ብለው በንቃት እንዲጠብቁ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ መከናወኑንም ጠቁመዋል።

ወጣቶች ተደራጅተው እንዲጠብቁ የማድረግ ሥራ መከናወኑን ጠቁመው፤ ባለሥልጣኑ እየሰራቸው ያሉ አሠራሮች ከሕብረተሰቡ ትብብር ጋር ተቀናጅተው ሕገ ወጥ ድርጊቶች እንዲቀንሱ ማስቻላቸውን ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ወንጀል የሆነውን ሕገ ወጥ የዱር እንስሳት ውጤቶች ዝውውር ከመቆጣጠር አኳያም፤ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአነፍናፊ ውሻዎች ጭምር የቁጥጥር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በአነፍናፊ ውሻዎች ታግዞ እየተሠራ ያለው የቁጥጥር ሥራ ውጤታማ መሆኑን አንስተው፤ በዚህም በሕገ ወጥ መንገድ የሚደረግ የእንስሳት ውጤቶች ዝውውር ቀንሷል ነው ያሉት።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026