🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ቴሌብር ተጠቃሚዎች በቀላሉ የፋይናንስ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ የፋይናንስ ተደራሽነትና አካታችነትን ለማስፋት ማስቻሉን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ።
ኢትዮ ቴሌኮም ከአዋሽ ባንክ ጋር በመተባበር "ጥላ" የተሰኘ አዲስ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት በቴሌብር አማካኝነት አስጀምሯል።
ይህ ትብብር የሀገሪቱን የፋይናንስ አካታችነት ለማስፋት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ኢትዮ ቴሌኮም የሀገሪቷን ዲጂታል ኢትዮጵያ ራዕይ እውን ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል።
ቴሌብርን በመጠቀም በቀላሉ የፋይናንስ አገልግሎት ማግኘት መቻሉን አመልክተው፤ ይህም ለተጠቃሚዎቹ ምቹ፣ ፈጣን እና ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ ተደራሽነት እንዲሰፋ ማድረጉን አንስተዋል።

ቴሌብር የቴክኖሎጂ አቅምን ከባንክ ተቋማት የፋይናንስ ልምድ ጋር የተጣመረበት መሆኑን ጠቅሰው፤ የፋይናንስ አገልግሎትን ወደ ህብረተሰቡ በስፋት እንዲደርስ እያደረገ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
ከአዋሽ ባንክ ጋር የተደረገው አጋርነትም ሁለቱ ተቋማት የየራሳቸውን ጥንካሬ ለሀገራዊ ልማት ለማዋጣት እንደሚያስችላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ አስረድተዋል።
"ጥላ" ዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ምቹ፣ ፈጣን እና ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ አገልግሎት የበለጠ ለማስፋት እንደሚረዳ ተናግረዋል።
የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፀሀይ ሽፈራው በበኩላቸው፤ "ጥላ" የባንኩን የዲጂታል ለውጥ ለማፋጠን የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም በቴሌብር በኩል የሚቀርቡት እንደ ማይክሮ ብድር (Micro Credit)፣ የሞባይል ቁጠባ (Mobile Saving) አገልግሎቶች ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው እና አነስተኛ ንግድ ለሚሰሩ ትልቅ ዕድል ይፈጥራሉ ብለዋል።
በቀጣይም ሁለቱ ተቋማት ተጨማሪ አዳዲስ እና ፈጠራ ያላቸው የፋይናንስ አገልግሎቶችን በማጠናከር እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።
"ጥላ" የፋይናንስ ዲጂታል አገልግሎት የቁጠባ፣ የግለሰብ ብድር፣ ለአነሰተኛ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ብድር እና የዲቫይስ ፋይናንስ አገልግሎቶች በአንድ ጥላ ስር ለመስጠት የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026