የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነርሽፕ ስልጠናዎች ችግር ፈቺ የፈጠራ ውጤትና መፍትሔ እያስገኙ ነው

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነርሽፕ ስልጠናዎች ችግር ፈቺ የፈጠራ ውጤትና መፍትሔ እያስገኙ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ፡፡

የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት በማስመልከት የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።

ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንት የዘርፉ ተዋንያን ንቁና ብቁ ተሳትፎ በማድረግ ችግር ፈቺ የፈጠራ ውጤቶች ላይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ለማበረታታት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በዚሁ ጊዜ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ፤ መንግስት የኢትዮጵያን የኢንተርፕርነርሽፕ ምኅዳር ለማስፋት በከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

ባለፉት ሰባት ዓመታትም የኢንተርፕርነርሽፕ ሥነ-ምህዳሩን ማስፋት የሚያስችሉ የአሰራርና የተቋማት የሪፎርም አጀንዳ በመቅረጽ ወሳኝ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ኢንተርፕርነሪያል መንግስት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህም ከባህላዊ የአሰራር ሥረዓት ጠባቂነት በመላቀቅ ንቁ፣ ችግር ፈቺ እና ዕድል ፈጣሪ መሆን እያስቻሉት መሆኑን ተናግረዋል።


በዚህም መንግስት ውጤታማ የመፍጠንና መፍጠር የአገልግሎት ሥርዓትን በመዘርጋት ስኬት እየተመዘገበ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የመንግስትን የአሰራር ስርዓት በፈጠራ የታገዘ እንዲሆን የፐብሊክ ሰርቪስ ኢኖቬሽን ላቦራቶሪ በማቋቋም አገልግሎቶችን የማሳለጥ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከተቋቋመ ጀምሮም የኢንተርፕርነር ስልጠና አቅሞችን በማሳደግ በአንድ ጊዜ በርካታ ዜጎችን የማሰልጠን አቅም እየዳበረ መምጣቱን አስረድተዋል።

ኢትዮጵያውያን ኢንተርፕርነሮችን በዓለም አቀፍ ውድድሮች ብቁና ንቁ ተወዳዳሪ በማድረግ ሀገራቸውን ከድህነት የሚያወጡ ዜጎችን ማፍራት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ማህበረሰብ አካል እንድትሆንም የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም ባለፈው ዓመት በተደረገው ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት ውድድር ላይ ኢትዮጵያ በ8ኛ ደረጃ ማጠናቀቅ አንዳስቻላት አስታውሰዋል።

በኢትዮጵያ የኢንተርፕርነር ስልጠናዎች ችግር ፈቺ የፈጠራ ውጤትና መፍትሔ እያስገኙ መሆኑን ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንት የፈጠራ አቅሞችን ማጎልበት የሚያስችል መድረክ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026