የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም ነው 

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት ቀይሮ ወደ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቀድሞ ሕንፃ በተዛወረበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) መልዕክት አስተላልፈዋል።

በዚሁ ወቅትም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአምስት ዓመት ውስጥ አሁን በሚገኝበት ደረጃ ላይ መድረሱ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ የሚታይ ተቋም መሆኑን ገልጸው፤ የሮቦቶችን ሶፍትዌር ብቻ ሳይሆን ውጫዊ የአካል ክፍልን (ሃርድዌር) መሥራት ጀምሯል ብለዋል።

ድሮን ማምረት ብቻ ሳይሆን የማነጋገር ዐቅም እየፈጠረ ያለ ተቋም መሆኑንም ተናግረዋል።


አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ ደረጃ የሚወዳደር አሠራርን የሚከተል መሆኑን ጠቁመው፤ በርካታ ምርቶችን አውጥቷል ብለዋል።

በጤናው ዘርፍ የጡት ካንሰር ልየታ ላይ ትልቅ ውጤት ማምጣት መቻሉን እና ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ በአርቲፊሻል ዐዋቂዎች ዘንድ ተቀባይነት ብሎም የባለቤትነት መብት ያገኘ ሥራ ነው ብለዋል።

በግብርና ዘርፍም የቡናና የሌሎች አዝርዕቶች በሽታ የሚለይ ፕሮዳክት መመረቱን በመጠቆም ለዚህም ባለቤትነት መብት መኖሩን አስረድተዋል።

በሌላ በኩል መሶብ የሚባለውን በአንድ ማዕከል ከ100 በላይ አገልግሎቶች የሚሰጠውን ሲስተም የገነባው አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መሆኑን አስታውቀዋል።

ገንዘብ ሚኒስቴር፣ገቢዎች ሚኒስቴር እና ጉምሩክ ኮሚሽንን ጨምሮ ተቋማት አሠራሮቻቸውን ለማዘመን የሚገለገሉባቸው በርካታ ሲስተሞችን መገንባት መቻሉን አንስተዋል።

የኢንስቲትዩቱ ሞቶ ኤ አይ ለሁሉም ስለሆነ፤ ከዚህ አንጻር አንዱ ማሳያ ክላውድ ኮምፒቲንግ መሆኑን አንስተዋል።


ለምሳሌ ከዳታ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ አማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ፣ ትግርኛ እና አፋርኛ የአንዱ ቋንቋ ተናጋሪ ሦስተኛ ሰው ሳያስገባ ከሌላኛው ቋንቋ ተናጋሪ ጋር መግባባት የሚችልበትን መንገድ፣ በጽሑፍ የገባን መልዕክት ወደ ድምጽ የመቀየር፣ በድምጽ ያለ መልዕክትን ወደ ጽሑፍ የመቀየርና መሰል አገልግሎት ለመስጠት በሺህ ሰዓቶች የሚቆጠሩ ኦዲዮዎችን ዳታዎች በማስገባት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።

የግብርና ሪቮሉሽን አንድ ሁለት ሦስት እያለ መጥቷል እኛ እዛ ውስጥ አልነበርንም፤ ቴክኖሎጂካል ሪቮሉሽን ነበሩ፣ ኢንደስትሪያል ሪቮሉሽኖች ነበሩ፤ በእነዚህ ሁሉ ኢትዮጵያ በሬና ሰውን ማላቀቅ ሳትችል የኖረችበት ዋናው ምክንያት አዲስ ዕውቀት፣ አዲስ ልምምድ፣ አዲስ ፈጠራ ሲፈጠር ያንን ነገር ለማወቅና ለመከተል የነበረው ጉጉት፣ ዝግጁነት እና እሳቤ አናሳ ስለነበረ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

እዚህ ላይ ለመተካከል ሳይሆን ጥሩ ተከታይ ለመሆን እንኳ በእጅጉ ይቀረን ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አሁን ሁኔታው መቀየሩን በአጽንኦት አስረድተዋል።

ስለዚህ ብንፈልግም ባንፈልግም ራሳችንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት ውስጥ ማስገባት ካልቻልን ደረጃው የትም ቦታ ይሁን እንደ ሀገር እንደ ከዚህ ቀደሙ ከትላልቅ ሪቮሉሽኖች ወደ ኋላ እንቀራለን ሲሉ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026