🔇Unmute
አምቦ ፤ ህዳር 3/2018 (ኢዜአ)፡-በምእራብ ሸዋ ዞን በዘንድሮ የበጋ ወራት 466 ሺህ 750 ሄክታር መሬት በመስኖ እየለማ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
በጽህፈት ቤቱ የአትክልት ባለሙያ አቶ መላኩ ተፈራ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የከርሰ ምድርና የገፀ ምድር የውሃ ሃብትን በመጠቀም የመስኖ ልማት ስራት በስፋት የማከናወን ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በመስኖ እና የግብርና ግብዓት አጠቃቀም እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ስራዎች ላይ ለአምራቾች ግንዛቤ በመስጠት ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉን ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት በዘንድሮው ዓመት በዞኑ ከ400 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በእስካሁኑ ሂደትም ከ70 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ስለመሸፈኑ ጠቅሰው እቅዱን ለማሳካት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ ዓመት በሁለት ዙሮች ከሚካሄደው በበጋ መስኖ ልማት ከ26 ነጥብ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡
በዞኑ ባለፈው ዓመት በአንደኛና በሁለተኛ ዙር በመስኖ ከለማ መሬት 25 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከጽህፈት ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026