🔇Unmute
ሆሳዕና ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሆሳዕና ማዕከል ተገልጋዮች ገለጹ፡፡
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ሥራ መጀመሩ ይታወቃል።

የማዕከሉን የሥራ እንቅስቃሴ በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር በስፍራው በመገኘት ተገልጋዮችና የሚመለከታቸውን የሥራ ሃላፊዎች አነጋግሯል።
ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ዳንኤል በየነ፣ አቶ ደስታ ኤርቻዮ እና አቶ ደመቀ ሙሉነህ ፤ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።
አገልግሎቱ በአንድ ማዕከል በርካታ ጉዳዮችን ጨርሶ መውጣት ከማስቻሉ ባለፈ ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ጊዜና ገንዘብ ቆጣቢ መሆኑንም ተናግረዋል።
በመሆኑም መሰል የአገልግሎት ማዕከላትን በማስፋት በተገልጋዮች ላይ ሲደርስ የነበረን እንግልት እና የብልሹ አሰራር መንስኤዎችን ማስቀረት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።

የማዕከሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ከበደ ሻሜቦ፤ በማዕከሉ የተለያዩ ተቋማት 20 አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ በማዕከሉ የሚሰጡ አገልግሎቶች እየሰፋ ይሄዳሉ ብለዋል።
በማዕከሉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ብልሹ አሰራሮችን ለማስቀረት እያስቻለ በመሆኑ በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026