የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ ዘመናዊ፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎትን መስጠት ያስችላል

Nov 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር፤ ህዳር 2/2018 (ኢዜአ)፡- መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ ዘመናዊ፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎትን ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ተናገሩ።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪና የኢፌዴሪ ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አልማዝ መሰለ በከተማው የተገነባውን የሐረሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀምረዋል።


በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ባደረጉት ንግግር በመደመር መንግስት እይታ እና ተግባራዊ እንቅስቃሴ በሁሉም ዘርፎች እመርታ እያስመዘገብን እንገኛለን ብለዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ ዘመናዊ፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው ብለዋል።

የማዕከሉ ስራ መጀመር በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል ለመስጠት የሚያስችል እና የተገልጋዩን ማህበረሰብ ምልልስና የአገልግሎት ቆይታ ጊዜን የሚያሳጥር መሆኑን ጠቅሰዋል።

ማዕከሉ በክልሉ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የሚኖረው ፋይዳ የላቀ መሆኑንም ተናግረዋል።


በተለይ ተመጋጋቢ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን በአንድ ማዕከል በማሰባሰብ ለህብረተሰቡ የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳለጥ እንደሚያግዝ ነው የጠቆሙት።

የክልሉ መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማጎልበት የጀመረውን ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

የኢፌዴሪ ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አልማዝ መሰለ በበኩላቸው በስምንት ክልሎች፣ በሁለት የከተማ አስተዳደሮችና በፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከልን ጨምሮ 18 ማዕከላት ተገንብተው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ተናግረዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአንድ ቦታ ላይ በክብርና በቅልጥፍና አገልግሎት የሚገኝበትን ስርዓት የያዘና መንግስትና ህዝብን የሚያቀራርብ ትልቅ ስኬት መሆኑንም ተናግረዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች የተሻለ የዲጂታል አማራጮችን በመጠቀም በቀላሉ የፌዴራልና የክልል ተቋማት አገልግሎቶችን የሚያገኙበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ የሐረሪ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ ጆርዳን ኢስሃቅ ናቸው።

ማዕከሉ በበቁ ሰዎች የተደራጀና ዘመኑን በሚመጥን አስተሳሰብና በላቀ የስራ ተነሳሽነት እንዲሁም በቴክኖሎጂ ለማገልገል መገንባቱን ገልጸዋል።

በሐረሪ መሶብ አንድ ማዕከል የተለያዩ የፌዴራልና የክልሉ ተቋማት አገልግሎት የሚሰጡ ሲሆን ከ50 በላይ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል ማግኘት ያስችላልም ተብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026