🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት የድርድር አባልነት ድርድር አካል የሆነውንና ሦስተኛውን የሁለትዮሽ የገበያ ድርድር ከቻይና ጋር በማጠናቀቅ በጄኔቫ ተፈራርማለች።
ፊርማውን በተባበሩት መንግሥታት እና ጄኔቫ በሚገኙ ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የኢትዮጵያ አምባሳደር እና ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ፀጋአብ ክበበውና በዓለም ንግድ ድርጅት የቻይና አምባሳደር እና ቋሚ ተወካይ ሊ ዮንግጂ ፈርመውታል።
እዚህ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የተደረሰው ሀገራቱ መካከል ውጤታማ ውይይቶችና ቴክኒካል ድርድሮች ከተደረጉ በኋላ መሆኑም ተጠቁሟል።
ይህም የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጠናከር፣ ፍትሐዊ፣ ሁሉን አቀፍ እና ሕጎችን መሠረት ያደረገ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓትን ለማንበር ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል ተብሏል።
የዓለም ንግድ ድርጅት የድርድር አባልነት ድርድር አካል የሆነውን ይህን የሁለትዮሽ የገበያ ድርድር ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከቱርክዬ እና አርጀንቲና ጋር መፈራረሟ ይታወቃል።
በቀጣይም ከሌሎች ሀገራት ጋር ተመሳሳይ ድርድሮችን በማጠናቀቅ መፈራረም የሚያስችሉ ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026