🔇Unmute
አምቦ ፤ጥቅምት22/2018 (ኢዜአ)፡- በምእራብ ሸዋ ዞን በመኸር አዝመራ በ48 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የለማው የቢራ ገብስ እንክብካቤ እየተደረገለት ነው፡፡
በጽህፈት ቤቱ የአዝዕርት ልማት ባለሙያ አቶ ደጀኔ ደቡሼ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የቢራ ገብስን በኩታ ገጠም በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው፡፡
በዚህም በዞኑ በስፋት ከሚመረተው የጤፍና ስንዴ ልማት በተጓዳኝ አርሶ አደሩ የቢራ ገብስ እንዲያመርት የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
በመኸር አዝመራም በዘር ከተሸፈነው 48 ሺህ ሄክታር መሬት ከ1 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚገኝም አስረድተዋል።
ምርታማነቱን ለማሳደግም የተሻሻሉ የቢራ ገብስ ዝርያዎችን ማቅረብ፣ የግብዓት አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግና በኩታ ገጠም የማደራጀት ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል፡፡
የቢራ ገብስ ልማቱ ወልመራ፣ አዳ በርጋ ፣ ጅባት፣ ጀልዱ፣ ድሬ እንጪኒ፣ ኤጄሬና ኤጀርሳ ለፎ ወረዳዎች በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ዘንድሮ የአየሩ ጸባይ ለእርሻው ተስማሚ በመሆኑ ምርቱ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው በልማቱ ከ29 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አርሶ አደሩ ዘመናዊ የግብርና አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ እየሰራ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የቢራ ገብስ ምርታማነትን በሄክታር 37 ኩንታል ማድረስ መቻሉንም አስረድተዋል።
በአርሶ አደሮቹ ጥራቱን ጠብቆ የሚመረተው የቢራ ገብስ ለብቅል ፋብሪካዎች ግብዓት የሚውል ሲሆን ባለፈው ዓመትም የተሻለ ምርት መገኘቱን አስታውሰዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026