🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብብር ለልማት መስራት ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትግራይ ክልል ያለውን የሰላም ሁኔታ በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብብር ለልማት መስራት ይገባል ብለዋል።
በትግራይ ክልል ተጨማሪ ወጊያ እንዲካሄድ አንፈልግም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዚያ ይልቅ ተባብረን ሀገር ማልማት ነው የምንፈልገው ነው ያሉት።
ከዚያ ውጭ መንግስትን በሃይል ለመጣል ፍላጎት ካለ እሱ ፈጽሞ ሊሳካ አይችልም የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የሚመድበው በጀት ለልማት ሳይሆን ለታጣቂ እየዋለ ነው ሲሉም ገልጸዋል።
ይህ ትክክል እንዳልሆነ ጠቁመውም ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብብር ለልማት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026