🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፡-የኮሪደር ልማት ሥራችን ከፍተኛ የፈጠራ ዐቅም እና የኑሮ ዘዬ ለውጥ እያመጣ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ በሰጡት ማብራሪያም፤ ከፍተኛ የአመለካከት ለውጥ የመጣበት ሥራ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል።
ሰው ከልማዱ ጋር ለመፋታት ቢቸገርም በሂደት አዲሱን ዓለም ይቀበላል፤ ስለዚህ ሥራችንን እናጠናክራለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የኮሪደር ልማት ሥራችን ከፍተኛ የፈጠራ ዐቅም እና የኑሮ ዘዬ ለውጥ እያመጣ ነው ብለዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራው ብዙ ዐቅሞች እንዲወጡ ማስቻሉን ጠቁመው፤ለምሳሌ ከወንዝ ዳርቻዎች ልማት ጋር በተያያዘ የውጭ ሰዎች ከብዷቸው የተውትን የሀገራችን ሰዎች በብቃት እየሠሩት መሆኑን በአድናቆት አንስተዋል።
ከስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ሥራ ጋር በተያያዘም በአዲስ አበባ ብቻ ከ1 ሺህ በላይ አነስተኛ ስታዲየሞች ገንብተናል ብለዋል።
ይህ ማለትም ወጣቶችን ከጫት እና ከሽሻ ላይ ተሻምተን ወደ ኳስ ሜዳ እያስገባናቸው ነው ማለት ነው ሲሉ አብራርተዋል።
ዜጎችን ከድራፍት ቤት ተሻምተን ወደ ኳስ ሜዳ እያስገባን ነው፤በጋራ የእግር እንቅስቃሴ በማድረግ የቤተሰብ ቁርኝት እንዲያድግ አስችለናል።
የሚታይ ከተማ እየፈጠርን ነው፤እግር ኳስ ሜዳዎቹ በመጪዎቹ 10 ዓመታት ለብሔራዊ ቡድን ቁልፍ ተጫዋቾችን ለማፍራት ያግዛሉ።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026