🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 16/2018 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ አገራት የጣና ፎረም ምክረ ሀሳቦች በመተግበር ለአህጉሪቷ ለውጥ በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ የማላዊ የቀድሞ ፕሬዝዳንትና የጣና ፎረም የቦርድ አባል ጆይሴ ባንዳ ገለጹ።
በባህር ዳርና አዲስ አበባ ከተሞች ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው 11ኛው ከፍተኛ ደረጃ ጣና ፎረም ዛሬ ተጠናቋል።
"አፍሪካ በተለዋዋጩ ዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሀሳብ የተካሄደው ፎረም፤ በአፍሪካ ሠላምና ደህንነት ጋር በተያያዘ ያሉ ችግሮች፣ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ በትኩረት መክሯል።

አፍሪካ በኢኮኖሚ እንዴት ራሷን መቻል አለባት? ምን ዓይነት እርምጃዎች ያስፈልጋሉ? የሚሉ ጥያቄዎች ተነስተው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን፤ በአፍሪካ ያሉ ወጣቶችና ሴቶችን ጨምሮ አካታች ሥርዓት መዘርጋት ለነገ የሚባሉ ጉዳዮች እንዳልሆኑ በፎረሙ በሰፊው ምክክር ተካሂዶበታል።
የማላዊ የቀድሞ ፕሬዝዳንትና የጣና ፎረም የቦርድ አባል ጆይሴ ባንዳ በፎረሙ መዝጊያ ላይ እንዳሉት፤ 11ኛው የጣና ከፍተኛ ደረጃ ፎረም ስኬታማ ሆኖ ተጠናቋል።
የፎረሙ መሪ ሀሳብ አፍሪካ በተለዋዋጩ ዓለም ሥርዓት እንደ አህጉር ልንነጋገርበት የሚገባ ወቅቱን የጠበቀ ጽንሰ ሀሳብ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ወደ ዲጂታል የሚደረገው ሽግግር፣ የተፈጥሮ ሀብትን በፍትሃዊነት እና ዘላቂነት ተደራሽ ማድረግ ትኩረት የሚፈልግ ጉዳይ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተዋል።
ዓለም በፍጥነት እየተለወጠች መሆኑን አስታውሰው፤አፍሪካም እየተለወጠ ላለው የዓለም ሥርዓት የሚመጥን እንቅስቃሴ ማድረግ አለባት፤ ለዚህ ደግሞ በጣና ፎረም የሚቀርቡ ምክረ ሀሳቦችን ወደ ተግባር በመቀየር ረገድ ከአፍሪካ አገራት በቁርጠኝነት መሥራት ይጠበቃል ብለዋል።
አፍሪካ ለማሳካት ያስቀመጠቻቸው ውጥኖች ያለ ወጣቶች ተሳትፎ እውን ሊሆን እንደማይችል አመልክተው፤በአፍሪካ በሁሉም መስክ የሚከናወኑ ተግባራት ወጣቶችን ማዕከል ያደረጉ ሊሆኑ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በፎረሙ ላይ የተለያዩ አገራት መሪዎች፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ልዩ መልዕክተኞች ምሁራንን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026