የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የወጪ ንግዱን በከፍተኛ ሁኔታ እያነቃቃው ነው

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የወጪ ንግዱን በከፍተኛ ሁኔታ በማነቃቃት ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን በዘርፉ የተሰማሩ ማህበራት ገለጹ።

ኢትዮጵያ ከሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራ መግባቷ ይታወቃል።

ገቢራዊ ከተደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ መካከል የብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ማሻሻያ አንዱ ነው።

ማሻሻያው የውጭ ምንዛሪ ስርዓቱን ገበያ መር ማድረጉን ተከትሎ በወጪ ንግድ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶችን ተጠቃሚ እያደረጋችው ይገኛል።

ለአብነትም ቡና፣ አበባ፣ ሰሊጥ፣ የቅባት እህሎች፣ አትክልትና ፍራፍሬ በማምረት ለውጭ ገበያ ለሚያቀርቡ አካላት ማሻሻያው ትልቅ እርምጃ ነው ተብሏል።

የኢትዮጵያ ስጋ አምራቶችና ላኪዎች ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ ከሊፋ ሁሴን ለኢዜአ እንዳሉት፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በተለይ ለስጋ አምራችና ላኪዎች ትልቅ እድል ይዞ መጥቷል።

ማሻሻያው በተለይም ከውጭ ምንዛሪ ተመን ጋር ተያይዞ ማነቆ የነበሩ አሰራሮችን ማቃለል ማስቻሉን ገልጸዋል።

ማሻሻያው ከተደረገ በኋላ በወጪ ንግድ አፈፃፀም ላይ ከፍተኛ ለውጥ መታየቱን ያስታወቁት ሰብሳቢው፤ አሁን ላይ የማህበሩን ገቢ 67 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ነው የገለጹት።

በዚህም ባለፉት ሶስት ወራት 5ሺህ ሜትሪክ ቶን የስጋ ምርት በመላክ ከ27 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኝቱን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ አበባና አትክልት አምራቾችና ላኪዎች ማህበር ዋና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ዘውዴ በበኩላቸው፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ ማነቃቃቱን ገልፀዋል።

ከማሻሻያው በኋላ በአበባ ልማትና ምርቱን ለውጭ ገበያ በማቅረብ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶች ዘርፉን ለማስፋፋት ዕድል እንደተፈጠረላቸው አስታውቀዋል።

ሪፎርሙ በተለይም ከሆርቲካልቸር ኢንዱስትሪው በቅሬታ ይነሱ የነበሩ አሳሪ ፖሊሲዎችን ለመቀየር ሰፊ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልፀዋል።

ማሻሻያው በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ምርቶችን መላክ የሚያስችል ነው ያሉት አቶ ቴዎድሮስ፤ የተወሰዱት እርምጃዎች ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ እያገዙ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የወጪ ንግድ አፈፃፀሙን ቀጣይነት እንዲኖረው ማድረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም በገመገሙበት ወቅት ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከወጪ ንግድ ከ2 ነጥብ 48 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን መግለጻቸውም ይተዋሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026