🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡- በማኅበራዊ የመገናኛ መተግበሪያዎች አማካኝነት የማጭበርበር ወንጀሎች ፈጽመዋል የተባሉ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ እየሠራ መሆኑን የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ።
አንዳንድ በማጭበርበር ድርጊት ላይ የተሰማሩ ሰዎች ከግለሰቦች ዕውቅና እና ፈቃድ ውጭ በሞባይሎቻቸው ውስጥ በመግባት የግለሰቦቹን የማኅበራዊ መገናኛ መተግበሪያዎች (እንደ ዋትስአፕ እና ቴሌግራም የመሳሰሉትን) ምስጢራዊ መረጃዎች በመስረቅ የገንዘብ ማጭበርበር ድርጊት ላይ መሰማራታቸውን አገልግሎቱ ገልጿል።
ግለሰቦቹ የማኅበራዊ መገናኛ መተግበሪያዎችን ከተቆጣጠሩ በኋላ እውነተኛ የአካውንት ባለቤት በመምሰል በግለሰቦቹ ስልኮች ተመዝግበው ለሚገኙ ቤተሰቦች፣ ዘመዶች፣ ጓደኞች፣ እና የሥራ ባልደረቦች ገንዘብ እንደተቸገሩ የሚገልፅ የጽሑፍ መልዕክት በመላክ ለዚሁ የማጭበርበር ዓላማ ወደ ተዘጋጀ የባንክ አካውንት እንዲላክላቸው ያደርጋሉ ብሏል፡፡
የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት የደረሱትን ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ በወንጀል ድርጊቱ ላይ የተሳተፉ አካላትን በመለየት እና በመከታተል በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ከሚመለከታቸው ባለ ድርሻ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሠራ መሆኑን ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።
ሕብረተሰቡም ይህን የማጭበርበር ድርጊት ለመከላከል ወደ ስልኩ ለሚደርሱ መልዕክቶች ምላሽ ከመስጠቱ አስቀድሞ በተለያዩ መንገዶች የመልዕክቱን ትክክለኛነት በማረጋገጥ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል።
እንዲሁም ከሚመለከታቸው ተቋማት የሚተላለፉ የጥንቃቄ መልዕክቶችን በመከታተል ራሱን ከወንጀል ድርጊቶች እንዲጠብቅ እና ወንጀል ተፈፅሞ ሲገኝም ለሕግ አስከባሪ አካላት እንዲያሳውቅ ጥሪ አቅርቧል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026