የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በደሴ ከተማ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተጠናቀቀ ነው

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ ፤ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ በተያዘው ወር የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

በደሴ ከተማ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና የዲጂታል አሰራርን ለማስፋት እየተደረገ ያለውን ጥረት በተመለከተ ኢዜአ የከተማ አስተዳደሩን ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝን አነጋግሯል።

ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው በማብራሪያቸውም በከተማ አስተዳደሩ የህዝብን አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተጠያቂነት ያለበት ለማድረግ የተቀናጀ ጥረት በመደረግ ላይ መሆኑን አንስተዋል።

በተለይም የአገልግሎት እንግልትን ለማስቀረትና በአንድ ስፍራ ላይ በርከት ያሉ አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችል የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

አገልግሎቱን በተያዘው ወር አጋማሽ ላይ ለመጀመርም የግንባታ ማስተካከያ፣ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎችን ዝግጁ የማድረግ፣ የአገልግሎት መስጫ ግብዓቶችን የማሟላትና ብቁ የሰው ሃይል ዝግጁ እየተደረገ ነው ብለዋል።

በማእከሉ በተለይም የመሬት ነክ፣ ገቢዎች፣ ንግድ፣ የቴሌኮም አገልግሎት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የባንክ፣ የኢሜግሬሽንና ሌሎችም አገልግሎቶች ተጀምረው እየሰፋ የሚሄድ ይሆናል ብለዋል።


በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የደሴ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቃሲም አበራ፤ የሕብረተሰቡን የልማትና የአገልግሎት ፍላጎቶች መሰረት ያደረጉ ተግባራት በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ የተቀላጠፈ ለማድረግ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ወሳኝ መሆኑን በማንሳት አገልግሎቱን ለማስጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ተናግረዋል።

በከተማው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሲጀመር ለጊዜው በ39 የአገልግሎት አይነቶች ስራ የሚጀመር መሆኑን አንስተው አገልግሎቱ እየበዛና እየሰፋ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።

የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች ተግባራዊ በመደረግ ላይ መሆኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026