የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የጋራና የውክልና ገቢ አሰባሰብ ውጤታማ አፈጻጸም ፍትሐዊ የመሰረተ ልማት ሥርጭት እውን እንዲሆን እያደረገ ነው  

Oct 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018 (ኢዜአ)፡-የፌደራልና ክልል መንግስታት የጋራና የውክልና ገቢ አሰባሰብ ውጤታማ አፈጻጸም ፍትሐዊ የመሰረተ ልማት ሥርጭት እውን እንዲሆን እያደረገ እንደሚገኝ የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ ገለጹ።

የገቢዎች ሚኒስቴር ከፌዴራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደር የገቢ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ጋር ከመስከረም 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሲያካሂድ የቆየውን የውይይት መድረክ አጠናቋል።


የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ የወሰደችው የፖሊሲ ለውጥና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በገቢ አስተዳደር ስርዓቱ ላይ እመርታዊ ለውጥ እንዲመዘገብ እያደረገ ነው።

በዚህም ሀገራዊ ወጪን በራስ አቅም መሸፈን የሚያስችል የታክስ አስተዳደር አቅም በመገንባት ረገድ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።

የታክስ አስተዳደር ሥርዓቱ ለፌዴራል መንግስት፣ ለክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የሰጠው ግልጽ የተግባርና ኃለፊነት እርከን መኖሩን አስረድተዋል።

ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ጋር በተፈጠረ ተግባቦትም የኢትዮጵያን የታክስ አስተዳደር ውጤታማና ተምሳሌታዊ በሆነ መንገድ ማስቀጠል የሚያስችል ምኅዳር መፈጠሩን ተናግረዋል።

በዚህም በጋራና የውክልና ገቢ አሰባሰብ ላይ የተፈጠረው የተሻለ አፈፃጸም በሁሉም አካባቢዎች ላይ ፍትሐዊ የመሰረተ ልማት ሥርጭት እንዲረጋገጥ እያደረገ እንደሚገኝ አብራርተዋል።


ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የተወሰደው የማሻሻያ እርምጃም የፌዴራልና የክልል መንግስታትን እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮችን የገቢ መሰብሰብ አቅም በማጎልበት ገንቢ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አስረድተዋል።

በ2018 በጀት ዓመት የተያዘውን ሀገራዊ የገቢ ዕቅድ ለማሳካት፣ ዘላቂ የገቢ ዕድገትን ለማረጋገጥና በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከክልሎች ጋር በጋራ ለመስራት በውይይት መድረኩ መግባባት ላይ መደረሱን አንስተዋል።

ሀገራዊ የልማት ስራዎችን ለማሳካት ሙሉ አቅምን መጠቀምና ቅንጅታዊ ስራዎችን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።

ፍትሐዊ የታክስ አስተዳደር ስርዓት ለመዘርጋት የታክስ አወሳሰንና ሌሎች ስራዎችን ለማጎልበት የግንኙነት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026