🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ ለልማት የሚውለውን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን ጥረት እየተደረገ መሆኑን የከተማው አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ።
መምሪያው የ2018 የመጀመሪያው ሩብ ዓመቱን የእቅድ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ዛሬ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የመምሪያው ኃላፊ ጌታቸው አለበል እንደገለጹት፤በከተማ አስተደደሩ ከሚካሄደው የንግድ እንቅስቃሴ ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ ለልማት ለማዋል በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
በዚህም በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ብቻ ከ306 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ በከተማዋ ለሚካሄዱ የልማት ስራዎች ማዋል መቻሉን አንስተዋል።
የተሰበሰበው ገቢም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 30 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ብልጫ እንዳለው አብራርተዋል።
በከተማው ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የልማት ወጪን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉም ተመልክቷል።

የዛሬው የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ዓላማም በግብር አሰባሰቡ ላይ የታዩ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠል እና ክፍተቶችን ለይቶ በማረም በቀጣይ የተሻለ ለመፈጸም መሆኑ ተጠቁሟል።
በከተማዋ የመንቆረር ክፍለ ከተማ የግብር ባለሙያ ስመኘው ውቤ በበኩላቸው፤ ግምገማው ድክመትና ጥንካሬን በግልጽ ያሳየ በመሆኑ ለቀጣይ ስራችን ውጤታማነት ተነሳሽነትን ፈጥሮልናል ብለዋል።
በተለይም ለግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ስለግብር አስፈላጊነትና ሰርቶ ባገኘው ልክ አሳውቆ እንዲከፍል ተከታታይ ትምህርት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
ሌላኛው የዘርፉ ባለሙያ ያለም ዳኘ፤ የከተማዋን እድገት በማፋጠን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የገቢ አሰባሰብ ስራን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
በግምገማ መድረኩ ላይ የመምሪያው፣ የክፍለ ከተሞችና የየቀበሌዎች የገቢ ሰብሳቢ አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026