🔇Unmute
አምቦ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በ7 ሺህ 437 ሄክታር መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እየለማ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባለሙያ አቶ መንገዱ ጉርሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ትኩረት ተሰጥቶ ስራው እየተከናወነ ይገኛል።

በክረምቱ ወራትም በተከናወነ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ስራ የተሻለ ምርት ለማግኘት የሰብል እንክብካቤ እና ጥበቃ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዚህ ወቅትም በ7 ሺህ 437 ሄክታር መሬት ላይ ምርጥ የአቮካዶ ዝርያዎች፣ ማንጎ፣ አፕል፣ ፓፓያና ሙዝ እየለማ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ብርቱካን፣ ሎሚና ዘይቱን እንዲሁም ሌሎች የአትክልት አይነቶች እየለሙ መሆኑን ጠቅሰው በአጠቃላይ በአትክልትና ፍራፍሬዎች እየለማ ከሚገኘው መሬት 646 ሺህ ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን ተናግረዋል።

የታቀደውን ምርት ለማግኘት የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ከወረዳ እስከ ቀበሌ ድረስ የግብርና ባለሙያዎችን መድቦ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አውስተዋል።
በአትክልትና ፍራፍሬ እየለማ ከሚገኘው መሬት ውስጥ አንድ ሺህ 353 ሔክታር መሬት በኩታ ገጠም የለማ መሆኑን ገልጸዋል።

አትክልትና ፍራፍሬ በብዛት እየለማ ያለባቸው ወረዳዎች ዳኖ፣ ኖኖ፣ ቶኬ ኩታዬ፣ ምዳቀኝ፣ ግንደበረት፣ ሊባን ጃዊ እና ጅባት ወረዳዎች እንደሆኑም ገልጸዋል፡፡
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026