🔇Unmute
ነገሌ ቦረና ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡-በምስራቅ ቦረና ዞን በድርቅ ምክንያት የሚከሰትን የምግብ እህል እጥረት ችግር ለመፍታት ከ24 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት ታቅዶ ወደስራ መገባቱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ።
በጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ሊበን ቦሩ እንደገለጹት፣ በምስራቅ ቦረና ዞን በተደጋጋሚ በሚከሰት ድርቅ ምክንያት የምግብ እህልና የእንስሳት መኖ እጥረት ችግር ይከሰታል።
ችግሩን ለመቋቋም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት መጀመሩንና ይህም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የስንዴ ተረፈ ምርቱንም ለእንስሳት መኖ ለማዋል እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዘንድሮም በዞኑ ከዘጠኝ ወረዳዎች ውስጥ በስድስቱ የመስኖ ልማት በማከናወን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት ከታቀደው 24 ሺህ 793 ሄክታር መሬት 856 ሺህ 633 ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱንም አቶ ሊበን አስረድተዋል፡፡
ዘንድሮ በዞኑ በበጋ መስኖ ለማልማት የታቀደው መሬት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ4ሺህ 787 ሄክታር ብልጫ አለው ብለዋል።
በጽህፈት ቤቱ የመካናይዜሽን ምርት ግብአት አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ገመዳ ሀሰን ለመስኖ ልማቱ ከ4ሺህ ኩንታል በላይ የስንዴ ምርጥ ዘርና ከ27 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለአርብቶ አደሩ መከፋፈሉን ገልጸዋል፡፡
በዞኑ ሊበን ወረዳ የጎቢቻ ቀበሌ ነዋሪ ሀጂ ኢብራሂም ጡና በመስኖ ልማቱ ከተሳተፉ አርብቶ አደሮች መካከል አንዱ ናቸው፡፡

ሰፊ መሬት ቢኖረንም አካባቢያችን ዝናብ አጠር በመሆኑ ለበርካታ ዓመታት በእንስሳት እርባታ ሥራ ላይ ብቻ አሳልፈናል ብለዋል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በበጋ ወራት የጀመሩት የመስኖ ስንዴ ልማት ከራሳቸው ባለፈ ምርቱን ለገበያ በማቅረብ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በተያዘው ዓመትም ሁለት ሄክታር ተኩል መሬታቸውን በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት አቅደው ወደተግባር መግባታቸውን አስረድተዋል፡፡
በምስራቅ ቦረና ዞን ቆላማ ወረዳዎች ከመስከረም አጋማሽ እስከ ጥቅምት ወር የመኸር ዝናብ የሚጥልበት ወቅት ሲሆን ከዚህ ጎን ለጎን እስከ ታህሳስ ወር የሚዘልቅ የበጋ መስኖ ልማት እንደሚካሄድ ከዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያሳያል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026