የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ዘላቂ የገቢ እድገትን ለማረጋገጥና የዘርፉን ችግር ለመፍታት የሪፎርም ስራዎችን ማጠናከር ይገባል

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦ ዘላቂ የገቢ እድገትን ለማረጋገጥና የዘርፉን ችግር ለመፍታት የሪፎርም ስራዎችን ማጠናከርና በጋራ መስራት እንደሚገባ የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ ገለጹ።

የገቢዎች ሚኒስቴር ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 1 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከሀገራዊ የገቢ ዘርፍና ቁልፍ ከሆኑ የፌዴራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደር ባለድርሻ አካላት ጋራ ሀገራዊ ውይይት እያካሄደ ይገኛል።


በውይይቱ ሚኒስቴሩ አመራር አባላት፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ሲሆን፤ መድረኩ በ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀምና በ2018 በጀት ዓመት እቅድ ላይ የሚመከርበት መሆኑ ተገልጿል።

በፊዚካል ፌዴራሊዝም ፖሊሲ አፈፃፀምና በገቢ ግብር አዋጅ አተገባበር ላይ መግባባት የሚደረስበት መድረክ ነው ተብሏል።

በዚሁ ወቅት የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት የገቢ ዘርፍ የተሻለ አፈፃፀም እንዲኖረው ለግብር ከፋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።

ለታክስ ህግ ተገዢ ህብረተሰብ ለመፍጠርና የታክስ ህግን አውቆ የሚያስተገብር የሰው ኃይል ለመገንባት የተጀመረውን ሪፎርም ከፌዴራል እስከ ክልል በወጥነት መተግበር እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

በዚህም የ2018 በጀት ዓመት ሀገራዊ የገቢ እቅድን በማሳካት ዘላቂ የገቢ እድገትን ለማረጋገጥና የዘርፉን ችግር ለመፍታት በጋራ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የፌዴራልና የክልል የገቢ ተቋማት በህገ ወጥ ንግድ ላይ ተገቢውን ክትትል ማድረግና ከሚመለከታቸው የህግ አስከባሪ ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት አለባቸው ብለዋል።

ከታክስ መረቡ ውጪና በታክስ መረቡ ውስጥ ሆነው ህገ ወጥ ተግባር የሚፈፅሙትን ስርዓት ማስያዝና የዜጎችን ሞራል መገንባት እንደሚጠበቅም አብራርተዋል።

ኢኮኖሚዊው የሚያመነጨውን ገቢ መሰብሰብ አገራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አንስተው፤ የአገር ውስጥ ሀብት የማሰባሰብ ስራን አጠናክሮ መተግበር እንደሚገባም ተናግረዋል።

በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ስርዓት ማጣጣምና የክልሎች ድጋፍ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ አበበ በበኩላቸው፤ በገቢ ዘርፉ በተደረገው ሪፎርም ሀገር አቀፍ የገቢ አፈፃፀምን ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም የገቢ አፈፃፀም በ2011 በጀት ዓመት ከነበረበት 277 ቢሊዮን ብር በላይ በ2017 ወደ አንድ ነጥብ አራት ትሪሊዮን ብር ማሳደግ መቻሉን አስታውቀዋል።

በ2018 በጀት አመት የታቀደውን ከሁለት ትሪሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ በዘርፉ የሚታዩ የአሰራርና የቅንጅት ችግሮችን በትብብር መፍታተ ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026