🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መስከረም 19/2018(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ ማኅበራት የተሳለጠ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲፈጠር እያደረጉ እንደሚገኝ የከተማ አስተዳደሩ የትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ያብባል አዲስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የነዋሪዎችን የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የአቅርቦት ፍላጎት ለማሳለጥ የተሻለ የአሰራር ሥርዓት እየተፈጠረ ነው።
የመንገድ ደኅንነትና የትራፊክ መጨናነቅን ለመቀነስም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት የታክሲ ተራ አስከባሪ በመባል የሚታወቀውን አደረጃጀት በአዲስ መልክ በተደራጀው የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ አማካኝነት የተሻለ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን አንስተዋል።
በተርሚናል ኢንተርፕራይዝ የተደራጁ አስተባባሪዎችም የትራፊክ መጨናነቅና የተሳፋሪዎችን እንግልት በመቀነስ የተሳለጠ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ በመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እያበረከቱ መሆኑን ገልጸዋል።
በአዲሱ የትራንስፖርት አስተባባሪዎች የተርሚናል ኢንተርፕራይዝም ግልጽና የአሰራር ሥርዓትን በተከተለ አግባብ በ87 ማኅበራት በማደራጀት የተሻለ አገልግሎት የሚሰጡበት ሁኔታ መፈጠሩን አስረድተዋል።
በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ አማካኝነት በአዲስ በተዋቀረው የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ የተደራጁ አስተባባሪዎችም የክህሎት ስልጠና ተሰጥቷቸው ወደስራ እንዲሰማሩ መደረጉን ገልጸው፤ የሚሰበስቡት ገንዘብ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓትን የተከተለ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢንተርፕራይዝ ማኅበራት አባላቱም ለሁለት ዓመታት በሚኖራቸው ቆይታ ዕድገት ተኮር በሆኑ ዘርፎች የሚሸጋገሩበት የቁጠባ ሥርዓት መዘርጋቱን አብራርተዋል።
በመዲናዋ የተደራጁ የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ ማኅበራትም የነዋሪዎችን የትራንስፖርት አገልግሎት በማሳለጥ ምቹ የትራፊክ ፍሰት በመፍጠር አዎንታዊ ሚና እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026