አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2017(ኢዜአ)፦ የጅግጅጋ ከተማ ኮሪደር ልማት የምስራቋን ኮከብ ወርቃማ የውበት ድባብ አልብሷታል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰተላለፉት መልዕክት ዛሬ በከተማዋ በምሽት ተዘዋውረን ባደረግነው ምልከታ ከስምንት ወራት በፊት በሁለት ምዕራፍ የተጀመሩ ስራዎች በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ መሆናቸውን አይተናል ብለዋል።
የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን የአስፋልት መንገዶች ያሰፋ፣ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶችንም ያካተተ ነው። የህዝብ መዝናኛ ቦታዎችን ትኩረት ተሰጥቷቸዋል ሲሉም ገልጸዋል።
የወጣቶችና ታዳጊዎች ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ የተሽከርካሪ ማቆሚያ፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ኃይል መሙያ ጣቢያዎችም በመገንባት ላይ ናቸው ነው ብለዋል፡፡
ከተማዋ ለክልሉ ከተሞች ሞዴል በሚሆን መልኩ ሰፊ የልማት ጎዳና ላይ ስትሆን የከተማዋ የቆየ ችግር የነበረውን ጎርፍ ለመከላከል የሚያስችሉ ማፋሰሻዎች፤ የተቀናጀ የውሃ፣ የመብራት፣ የቴሌኮምና የመንገድ መሠረተ ልማት ዝርጋታዎችም ይበሉ የሚያሰኙ ናቸው ሲሉም አክለዋል፡፡
በአጠቃላይ በከተማዋ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች ባለሀብቶች በከተማዋ በሆቴል አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ተሰማርተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታን እየፈጠሩ ይገኛሉ ሲሉ ነው የገለጹት በመልዕክታቸው፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025