
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ እና ጣሊያን የግብርና ትብብር ስምምነት ለምርታማነት ዕድገት ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ።
ኢትዮጵያ እና ጣሊያን በግብርናው ዘርፍ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) እና የጣሊያን ግብርና እና ምግብ ሉዓላዊነት ሚኒስትር ፍራንሲስኮ ሎሎ ብሪጅዳ ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ ኢትዮጵያ ምርታማነትን ለማሳደግ ለምታደርገው ጥረት ትልቅ አስተዋጽኦ የሚጫወት ነው ተብሏል።
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ ስምምነቱ፥ የቡና ዕሴት ሰንሰለትን ማሳለጥ፣ የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የቡና አምራች አርሶ አደሮችን መደገፍ እና የግብርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ያተኮረ መሆኑን አስታውቀዋል።
ጣሊያን ዘመናዊ ግብርናን በመተግበር ከፍተኛ ተሞክሮ እንዳላት የጠቀሱት የግብርና ሚኒስትሩ፥ ስምምነቱ የስልጠና እና የአቅም ግንባታ ስራዎችን ማካተቱን ተናግረዋል።
ጣሊያን ከአፍሪካ ሀገራት ጋር በግብርናው ዘርፍ በአጋርነት ለመሥራት ይፋ ባደረገችው ዕቅድ መሰረት ኢትዮጵያ ተጠቃሚ የሚያደርጋትን የመግባቢያ ስምምነት በቀዳሚነት መፈራረሟን አንስተዋል።
የጣሊያን ግብርና እና ምግብ ሉዓላዊነት ሚኒስትር ፍራንሲስኮ ሎሎ ብሪጅዳ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ እና ጣሊያን በትብብር 2ኛውን የተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤን በስኬት ማዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ስምምነቱ ለሁለቱ ሀገራት የግብርና ምርታማነት ዕድገት ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑንም ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026