አዳማ፤ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ)፦የጤፍ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን ተደራሽ ለማድረግ በምርምር የታገዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ገለጸ።
በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የጤፍ ምርት ከፍተኛ ተመራማሪ አብዲ ጁፋር (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለፁት፥ ኢንስቲትዩቱ የጤፍ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በምርምር የተደገፈ ስራ እየሰራ ነው።
ኢኒስቲትዩቱ በጤፍ ላይ ምርምር ማድረግ ከጀመረ አንስቶ እንደየአካባቢው የአየር ጸባይ ሁኔታ የጤፍ ምርትን ለማስፋፋትና የተሻለ ምርት ለማግኘት የሚያስችሉ ወደ 60 የሚጠጉ የጤፍ ዝርያዎች በምርምር መለቀቃቸውን ገልጸዋል።
በዚህም በቂ ዝናብ በሚያገኙ አካባቢያዎች ከ40 በላይ የተሻሻለ ዝርያ ያላቸው የጤፍ ዘር መለቀቁን ገልጸው፥ በዝናብ አጠር አካባቢዎች ደግሞ 15 እንዲሁም ለደጋ የአየር ጸባይ ሁለት ዝርያ፣ለመስኖ ልማት ተስማሚ የሆነ ደግሞ አንድ የጤፍ ዝርያ መለቀቁን አስረድተዋል።
ኢንስቲትዩቱ ከዝርያ ማሻሻል ስራ ጎን ለጎን የጤፍ ምርትና ምርታማነት ማሳደግ የሚያስችሉ የቴክኖሎጂና ኤክስቴንሽን አሰራሮችን ለመተግበር በምርምር የተደገፈ ስራ እያከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል።
በብሔራዊ የጤፍ ምርምር ፕሮግራም አማካኝነት በዘርፉ ያሉ ማነቆዎችንና መፍትሔዎች ዙሪያ ግብርና ሚኒስቴርን ጨምሮ ከሌሎች ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።
በኦሮሚያ፣አማራና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸው፥ በተለይም በምርምር የሚወጡ ቴክኖሎጂዎች በአግባቡ አርሶ አደሩ ዘንድ እንዲደርሱና በዘርፉ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።
የምርምር ስራውን የበለጠ ለማጠናከር ለተመራማሪዎች፣ ለቴክኒሺያኖችና ለረዳት የመስክ ተመራማሪዎች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ገልጸዋል።
ጤፍ የስነ ምግብ ስርዓት የሚፈልገውን ንጥረ ነገሮችን የያዘ በመሆኑ የሀገር ውስጥ ፍጆታን ሳይነካ በዓለም እንዲታወቅ ጭምር ግብ ተቀምጦ የምርምር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል።
በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ለማ በበኩላቸው፥ በምርምር የወጡ የጤፍ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ቴክኖሎጂዎች ለአርሶ አደሮች ተደራሽ እንዲሆኑ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህም ባለፈ ቴክኖሎጂዎቹ ውጤት እንዲያመጡ በኤክስቴንሽን አገልግሎት የተደገፉ ስራዎችን ከማጠናከር ጀምሮ ከኢንስቲትዩቱ ጋር ቅንጅታዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025