የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የ2018 በጀት አመት የበለጠ ውጤታማ ለመሆን የምንሰራበት ነው -ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jul 22, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ14/2017(ኢዜአ)፡-የ2018 በጀት አመት ከተጠናቀቀው በጀት አመት የበለጠ ስኬት ለማስመዝገብ በትኩረት የምንሰራበት ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2017 በጀት አመት ውጤታማ ለሆኑ ተቋማት ዕውቅና እና ሽልማት አበርክቷል።

በዚህም ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማት፣ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች የመኪና እና የምስክር ወረቀት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፥ ከተማ አስተዳደሩ በ2017 በጀት አመት ከፍተኛ አፈጻጸም በማስመዝገብ ውጤታማ ሆኗል።

ውጤቱ የተገኘው ጠንክሮ በመስራት መሆኑን የጠቆሙት ከንቲባዋ፤ ስኬት ያስመዘገቡትን እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ለበለጠ ስራ እንዲተጉ አሳስበዋል።

ተቋማቱ የከተማዋ ልማት እንዲፋጠንና የነዋሪዎቿ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ጠንክረው መስራታቸውን አስታውቀዋል።

የዕውቅና መርኃ ግብሩ ከፍተኛ ውጤት ያመጡትን ይበልጥ የሚያበረታታ ሌሎችንም በቁጭት የሚያነሳሳ መሆኑን አንስተዋል።

የ2018 በጀት አመት የበለጠ ውጤታማ ለመሆን የምንሰራበት ነው ያሉት ከንቲባዋ፥ ዕውቅናው ለቀጣይ ስራ ስንቅ እንደሚሆን ነው ያስታወቁት።

ሽልማት እና ዕውቅና የተሰጣቸው ተቋማት፣ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች በበኩላቸው፥ የተሰጣቸው እውቅናና ሽልማት በቀጣይ ጠንክረው በመስራት የበለጠ ውጤታማ ለመሆን እንደሚያነሳሳቸው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.