
አዲስ አበባ፤ሐምሌ14/2017(ኢዜአ)፡-የ2018 በጀት አመት ከተጠናቀቀው በጀት አመት የበለጠ ስኬት ለማስመዝገብ በትኩረት የምንሰራበት ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2017 በጀት አመት ውጤታማ ለሆኑ ተቋማት ዕውቅና እና ሽልማት አበርክቷል።
በዚህም ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማት፣ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች የመኪና እና የምስክር ወረቀት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፥ ከተማ አስተዳደሩ በ2017 በጀት አመት ከፍተኛ አፈጻጸም በማስመዝገብ ውጤታማ ሆኗል።
ውጤቱ የተገኘው ጠንክሮ በመስራት መሆኑን የጠቆሙት ከንቲባዋ፤ ስኬት ያስመዘገቡትን እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ለበለጠ ስራ እንዲተጉ አሳስበዋል።
ተቋማቱ የከተማዋ ልማት እንዲፋጠንና የነዋሪዎቿ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ጠንክረው መስራታቸውን አስታውቀዋል።
የዕውቅና መርኃ ግብሩ ከፍተኛ ውጤት ያመጡትን ይበልጥ የሚያበረታታ ሌሎችንም በቁጭት የሚያነሳሳ መሆኑን አንስተዋል።
የ2018 በጀት አመት የበለጠ ውጤታማ ለመሆን የምንሰራበት ነው ያሉት ከንቲባዋ፥ ዕውቅናው ለቀጣይ ስራ ስንቅ እንደሚሆን ነው ያስታወቁት።
ሽልማት እና ዕውቅና የተሰጣቸው ተቋማት፣ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች በበኩላቸው፥ የተሰጣቸው እውቅናና ሽልማት በቀጣይ ጠንክረው በመስራት የበለጠ ውጤታማ ለመሆን እንደሚያነሳሳቸው ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026