
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 13/2017(ኢዜአ)፦ በመዲናዋ በየዘርፉ ለተመዘገቡ ስኬቶች ከህዝቡ ጋር ተቀራርቦ መስራቱ ጉልህ ሚና መጫወቱን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከተማ አስተዳደሩ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት ዛሬም ቀጥሎ ተካሂዷል።
በውይይቱ የተከናወኑ ተግባራት፣ የተገኙ ስኬቶች፣ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይ ከውይይቱ ተሳታፊዎች ጥያቄዎች ተነስተው በመዲናዋ ከፍተኛ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የነዋሪውን ተጠቃሚነት ከፍ ያደረጉ ስራዎች ተከናውነዋል።
በተለይም ህብረተሰብን በማሳተፍ በርካታ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደ አገልግሎት ማስገባት መቻሉን ጠቅሰው፤ ውጤቱ ከተማ አስተዳደሩ ህዝብን በማሳተፍ ስኬታማ ስራ እያከናወነ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል።
በበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ በአቅመ ደካሞች ቤት ዕድሳት፣ በማዕድ ማጋራት የተገኙ ስኬቶች ተጠቃሽ መሆናቸውንም አብራርተዋል።
የሰው ተኮር ተግባራትን ማጠናከር ከዋና ዋና ተልዕኮዎች አንዱ መሆኑን የገለጹት ከንቲባዋ፤ በዚህ ረገድ ይበልጥ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ መትጋት አለብን ብለዋል።

የኑሮ ውድነትን መቀነስና በመሰረተ ልማት አቅርቦት ላይ አበረታች ውጤቶች መኖራቸውን ጠቅሰዋል።
ከማህበረሰቡ የልማት ፍላጎት አኳያ አሁንም ብዙ መስራት ይጠበቅብናል ያሉት ከንቲባ አዳነች የስራ ባህልን ማሻሻል፣ የተቋም ግንባታ ማጠናከር፣ አገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻል ከቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል እንደሚገኙበት ገልፀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር የምርት አቅርቦት እንዲጨምር እየተሰራ ያለው ስራ መቀጠሉን ተናግረዋል።
ሸማቹ የፍጆታ ምርቶችን በቀጥታ ከአምራቹ የሚያገኝባቸው ማዕከላት ተገንብተው ወደ ስራ መግባታቸውንም ገልጸዋል።
በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሞገስ ባልቻ፤ በአመራሩ ረገድ የድጋፍ እና

ክትትል ባህል መዳበሩ ለተገኘው ውጤት አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026