
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 12/2017 (ኢዜአ):-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተጠናቀቀው የ2017 በጀት አመት የህብረተሰቡን የልማት ፍላጎት ያሳኩ ስራዎች መከናወናቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት ማካሄድ ጀምሯል።
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈጉባኤ ቡዜና አልከድር፣በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ሞገስ ባልቻ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎቾ ተገኝተዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የ2017 በጀት አመት ስኬታማ አመት መሆኑን ገልጸው፥አጠቃላይ የእቅድ አፈጻጸሙ 95 በመቶ ነው ብለዋል።
በበጀት አመቱ የህብረተሰቡን የልማት ፍላጎት ያሳኩ ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውንም ተናግረዋል።
የተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች ትርጉማቸው ከፍ ያለ መሆኑን አንስተው፤ በርካታ ህዝብ በጋራ የሚገለገልባቸው ስራዎች መሆናቸውንም ገልጸዋል።
የኑሮ ውድነትን ለመቆጣጠር በልዩ ትኩረት በርካታ ምርቶችን ወደ ከተማው እንዲገቡ በማድረግ ገበያን የማረጋጋት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል።
ከስራ እድል ፈጠራ አንጻር ከእቅድ በላይ መከናወኑን የገለጹት ከንቲባዋ፤ ከገቢ አሰባሰብ አኳያም ጠንካራ ስራ መሰራቱን ነው የጠቀሱት።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተከናወኑ ተግባራት በከተማዋ ባሉ ኢንዱስትሪዎች ላይ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን አንስተው፤ በዚህም ምርትና ምርታማነታቸው ማደግ ችሏል ብለዋል።
በኮሪደር ልማት የከተማዋን ጽዳት፣ውበት እንዲሁም ገጽታ በከፍተኛ ሁኔታ መቀየር መቻሉን ገልጸዋል።
ይህም ከተማዋን ለኑሮ ምቹና ቱሪዝምን በከፍተኛ መጠን የምትስብ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት።
ከብልጽግና መዳረሻ እና ከህዝቡ የልማት ፍላጎት አንጻር የተከናወኑ ስራዎች በቂ አለመሆናቸውን ያነሱት ከንቲባዋ፤ በ2018 በጀት አመት ከስኬቶች ትምህርት በመውሰድ ዘላቂ ለማድረግ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026