የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በዞኑ አርሶ አደሮች አሲዳማ አፈርን በማከም ምርታማነታቸውን ማሳደግ ችለዋል

Jul 21, 2025

IDOPRESS

ደብረማርቆስ፤ ሐምሌ 11 /2017(ኢዜአ)፡ - በምሥራቅ ጎጃም ዞን አርሶ አደሮች አሲዳማ አፈርን በኖራ አክመው የእርሻ ማሳቸውን በማልማት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻላቸው ተገለጸ።

ዘንድሮ ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል ትኩረት ከተሰጠው ጉዳይ አሲዳማ አፈርን በማከም ማልማት እንደሆነ የዞኑ ግብርና መምሪያ አመልክቷል።

ከ248 ሄክታር በላይ መሬት በኖራ ለማከም ታቅዶ እስካሁን ከ48ሺህ ኩንታል በላይ ኖራ በማቅረብ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ መበተኑን መምሪያው ጠቅሷል።

አርሶ አደር መልሳቸው ያዜ በዞኑ የማቻከል ወረዳ የቅዳማን ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ፤ በአሲዳማ አፈር የተጠቃ አንድ ሄክታር የእርሻ ማሳቸውን በኖራ በማከም ምርታማነታቸውን ማሳደግ እንደቻሉ ለኢዜአ ተናግረዋል።

ይህም የመሬታቸውን ለምነት በመጨመሩ በሄክታር ከአምስት ኩንታል በላይ የምርት ጭማሪ ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል።

በተያዘው የመኸር ወቅትም ተግባሩን ለማስቀጠል ጠንክረው እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል።

በአነደድ ወረዳ የጉዳለማ ቀበሌ አርሶ አደር ተመስጌን ክብረት በበኩላቸው፤ ግማሽ ሄክታር ማሳቸውን በኖራ በማከም የአፈሩ ለምነት እንዲመለስ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

ቀደም ሲል በአሲድ የተጠቃው ማሳቸው ምርቱ መቀነሱን አውስተው፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተጠቃው ማሳቸው በኖራ አክመው በመዝራት የጤፍና የስንዴ ምርታቸው ላይ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ተናግረዋል።ያገኙትን ጥቅም ለማሳደግም ከዘር በፊት ቀደም ብለው ኖራ በመበተን ማከማቸውን አንስተዋል።

የምሥራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አበበ መኮንን እንደገለጹት፤ ዘንድሮ ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል ትኩረት ከተሰጠው ጉዳይ አሲዳማ አፈርን በማከም ማልማት ነው።


ለዚህም በዞኑ ከ248 ሄክታር በላይ መሬት በኖራ ለማከም ታቅዶ እስካሁን ከ48ሺህ ኩንታል በላይ ኖራ በማቅረብ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ መበተኑን ተናግረዋል።

አርሶ አደሮችን በማሳተፍ እየተካሄደ ያለው አሲዳማ አፈርን በኖራ የማከም ተግባር ውጤታማነቱ በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን አስረድተዋል።

ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ እንደሚያመልክተው፤ በምሥራቅ ጎጃም ዞን በ2017/2018 የምርት ዘመን ከ642 ሺህ ሄክታር በላይ በሰብል ዘር በመሸፈን ከ25 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026