
ደብረማርቆስ፤ ሐምሌ 11 /2017(ኢዜአ)፡ - በምሥራቅ ጎጃም ዞን አርሶ አደሮች አሲዳማ አፈርን በኖራ አክመው የእርሻ ማሳቸውን በማልማት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻላቸው ተገለጸ።
ዘንድሮ ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል ትኩረት ከተሰጠው ጉዳይ አሲዳማ አፈርን በማከም ማልማት እንደሆነ የዞኑ ግብርና መምሪያ አመልክቷል።
ከ248 ሄክታር በላይ መሬት በኖራ ለማከም ታቅዶ እስካሁን ከ48ሺህ ኩንታል በላይ ኖራ በማቅረብ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ መበተኑን መምሪያው ጠቅሷል።
አርሶ አደር መልሳቸው ያዜ በዞኑ የማቻከል ወረዳ የቅዳማን ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ፤ በአሲዳማ አፈር የተጠቃ አንድ ሄክታር የእርሻ ማሳቸውን በኖራ በማከም ምርታማነታቸውን ማሳደግ እንደቻሉ ለኢዜአ ተናግረዋል።
ይህም የመሬታቸውን ለምነት በመጨመሩ በሄክታር ከአምስት ኩንታል በላይ የምርት ጭማሪ ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል።
በተያዘው የመኸር ወቅትም ተግባሩን ለማስቀጠል ጠንክረው እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል።
በአነደድ ወረዳ የጉዳለማ ቀበሌ አርሶ አደር ተመስጌን ክብረት በበኩላቸው፤ ግማሽ ሄክታር ማሳቸውን በኖራ በማከም የአፈሩ ለምነት እንዲመለስ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
ቀደም ሲል በአሲድ የተጠቃው ማሳቸው ምርቱ መቀነሱን አውስተው፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተጠቃው ማሳቸው በኖራ አክመው በመዝራት የጤፍና የስንዴ ምርታቸው ላይ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ተናግረዋል።ያገኙትን ጥቅም ለማሳደግም ከዘር በፊት ቀደም ብለው ኖራ በመበተን ማከማቸውን አንስተዋል።
የምሥራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አበበ መኮንን እንደገለጹት፤ ዘንድሮ ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል ትኩረት ከተሰጠው ጉዳይ አሲዳማ አፈርን በማከም ማልማት ነው።

ለዚህም በዞኑ ከ248 ሄክታር በላይ መሬት በኖራ ለማከም ታቅዶ እስካሁን ከ48ሺህ ኩንታል በላይ ኖራ በማቅረብ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ መበተኑን ተናግረዋል።
አርሶ አደሮችን በማሳተፍ እየተካሄደ ያለው አሲዳማ አፈርን በኖራ የማከም ተግባር ውጤታማነቱ በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን አስረድተዋል።
ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ እንደሚያመልክተው፤ በምሥራቅ ጎጃም ዞን በ2017/2018 የምርት ዘመን ከ642 ሺህ ሄክታር በላይ በሰብል ዘር በመሸፈን ከ25 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026