አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቴክኖሎጂ ግንባር ቀደም እንድትሆን ታዳጊዎችን በሰው ሰራሽ አስተውሎት እውቀት መቅረጽ እንደሚገባ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ገለፁ።
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በተለያዩ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፎች 4ኛውን የታዳጊዎች የክረምት ስልጠና በሳይንስ ሙዚየም አስጀምሯል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ታዳጊዎችንና ወጣቶችን ለማብቃት በክረምት ስልጠና እንዲሁም ከትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር እውቀትና ችሎታ እንዲያዳብሩ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ሀገራት ችግሮቻቸውን የሚፈቱበት ቁልፍ መሳሪያ እየሆነ መምጣቱን አንስተዋል።
በኢትዮጵያም ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም በሁሉም መስክ ቀዳሚ ለመሆን ታዳጊዎች ላይ መስራት ያስፈልጋል ነው ያሉት።
በዘርፉ መሰረታዊ እውቀት ኖሯቸው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
ኢንስቲትዩቱ ትኩረት ከሚሰጥባቸው ስራዎች መካከል በዘርፉ የሰው ሃይል ማጎልበትና ግንዛቤ መፍጠር አንዱ መሆኑን ገልፀው 4ኛ ዓመቱን የያዘው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የክረምት ስልጠናም ተጠቃሽ እንደሆነ አንስተዋል።
የስልጠና መርሃ ግብሩ ከ3 ዓመት በፊት በ15 ተማሪዎች እንደተጀመረ ገልፀው አሁን ላይ በርካታ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እየተመዘገቡበት እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በ4ኛው ዙር የክረምት ስልጠናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡ 3ሺህ ታዳጊዎች መካከል 300ዎቹ መስፈርቱን አሟልተው ወደ ስልጠና መግባታቸውን ገልጸዋል።
ስልጠናው ለሁለት ወራት የሚሰጥ ሲሆን፥ ታዳጊዎቹ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሰረታውያን፣ ሮቦቲክስ፣ ፕሮግራሚንግና ሌሎች ትምህርቶችን እንደሚወስዱም ተናግረዋል።
ከቴክኒካል ስልጠና ባሻገር ችግር ፈቺ፣ የቡድን ስራ፣ የስራ ፈጠራና የተግባቦት እና መሰል የህይወት ክህሎቶችን ማዳበር የሚያስችሏቸውን ስልጠናዎች እንደሚሰጣቸውም ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025