የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በሐረሪ ክልል 24 አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ ገብተዋል - ቢሮው

Jul 10, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል በ2017 በጀት ዓመት 24 አዳዲስ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መግባታቸውን የክልሉ ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ ወደ ስራ የገቡ ኢንዱስትሪዎች ለዜጎች የስራ እድል እየፈጠሩ መሆኑም ተገልጿል።

የክልሉ ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ ኡስማኢል ዩስፍ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ በተለይም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪውን የማምረት አቅም ከማጎልበት ባለፈ በዘርፉ መነቃቃት እንዲፈጥር እያስቻለ ነው።

በክልሉ ወደ ስራ የገቡት ኢንዳስትሪዎች ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶችን በማጎልበትና ተኪ ምርቶችን በማምረት የውጪ ምንዛሬን እያስቀሩና ከፍተኛ ሚና እያበረከቱ እንደሚገኙም ገልጸዋል።

በክልሉም በ2017 በጀት ዓመት ሰባት መካከለኛና 17 አነስተኛ አዳዲስ ኢንዳስትሪዎች ወደ ስራ መግባታቸውንና እነዚህም 383 ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል መፍጠራቸውን አክለዋል።

በተለይም ዘንድሮ በክልሉ ለአምራች እንዱስትሪዎች 579 ቶን የሚሆን ግብዓት መቅረቡን ጠቁመው ለአምራች እንዱስትሪዎቹ ከመሰረተ ልማት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን የመቅረፍ ስራ መከናወኑንም አመላክተዋል።

መንግስት የጀመረውን የአረንጓዴ ልማት ለማጎልበት ፋብሪካ ከፍተው የፕላስቲክ ፌስታል በከረጢት የመተካት ስራ መጀመራቸውን የተናገሩት ደግሞ የታቴ የከረጢት ፋብሪካ ባለቤት አቶ አቡበከር አዲል ናቸው።

ፋብሪካው በቀን ከ150ሺህ እስከ 200ሺህ ከረጢት እንደሚያመርት ጠቁመው በተለይም ለዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል እንደፈጠሩም ተናግረዋል።


በከተማው የሚገኘው የረሃ ፎም ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ ኡመር ሳሊህ በበኩላቸው በአልባሳት በኩል ተኪ ምርቶችን በማምረት ለአካባቢው ህብረተሰብና ተቋማት ለገበያ እያቀረቡ መሆኑ በመጥቀስ በቀጣይም ምርታቸውን በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል ለማዳረስ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በፋብሪካዎቹ የስራ እድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች እንደሚናገሩት የስራ እድል ተፈጥሮላቸው እራሳችውንና ቤተሰባቸውን ከመደጎም ባለፈ ልምድ እየቀሰሙና በትርፍ ጊዜያቸውም የኮሌጅ ትምህርት እንዲከታተሉ እድል እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።


በሐረሪ ክልል 165 ከፍተኛ፣ መካከለኛና አነስተኛ አምራች ኢንዳስትሪዎች በማምረት ስራ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.