
ሐረር፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል በ2017 በጀት ዓመት 24 አዳዲስ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መግባታቸውን የክልሉ ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ አስታወቀ።
በክልሉ ወደ ስራ የገቡ ኢንዱስትሪዎች ለዜጎች የስራ እድል እየፈጠሩ መሆኑም ተገልጿል።
የክልሉ ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ ኡስማኢል ዩስፍ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ በተለይም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪውን የማምረት አቅም ከማጎልበት ባለፈ በዘርፉ መነቃቃት እንዲፈጥር እያስቻለ ነው።
በክልሉ ወደ ስራ የገቡት ኢንዳስትሪዎች ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶችን በማጎልበትና ተኪ ምርቶችን በማምረት የውጪ ምንዛሬን እያስቀሩና ከፍተኛ ሚና እያበረከቱ እንደሚገኙም ገልጸዋል።
በክልሉም በ2017 በጀት ዓመት ሰባት መካከለኛና 17 አነስተኛ አዳዲስ ኢንዳስትሪዎች ወደ ስራ መግባታቸውንና እነዚህም 383 ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል መፍጠራቸውን አክለዋል።
በተለይም ዘንድሮ በክልሉ ለአምራች እንዱስትሪዎች 579 ቶን የሚሆን ግብዓት መቅረቡን ጠቁመው ለአምራች እንዱስትሪዎቹ ከመሰረተ ልማት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን የመቅረፍ ስራ መከናወኑንም አመላክተዋል።
መንግስት የጀመረውን የአረንጓዴ ልማት ለማጎልበት ፋብሪካ ከፍተው የፕላስቲክ ፌስታል በከረጢት የመተካት ስራ መጀመራቸውን የተናገሩት ደግሞ የታቴ የከረጢት ፋብሪካ ባለቤት አቶ አቡበከር አዲል ናቸው።
ፋብሪካው በቀን ከ150ሺህ እስከ 200ሺህ ከረጢት እንደሚያመርት ጠቁመው በተለይም ለዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል እንደፈጠሩም ተናግረዋል።

በከተማው የሚገኘው የረሃ ፎም ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ ኡመር ሳሊህ በበኩላቸው በአልባሳት በኩል ተኪ ምርቶችን በማምረት ለአካባቢው ህብረተሰብና ተቋማት ለገበያ እያቀረቡ መሆኑ በመጥቀስ በቀጣይም ምርታቸውን በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል ለማዳረስ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
በፋብሪካዎቹ የስራ እድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች እንደሚናገሩት የስራ እድል ተፈጥሮላቸው እራሳችውንና ቤተሰባቸውን ከመደጎም ባለፈ ልምድ እየቀሰሙና በትርፍ ጊዜያቸውም የኮሌጅ ትምህርት እንዲከታተሉ እድል እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።

በሐረሪ ክልል 165 ከፍተኛ፣ መካከለኛና አነስተኛ አምራች ኢንዳስትሪዎች በማምረት ስራ ላይ ናቸው።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026