
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ የተገበርነው ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ፖሊሲ ወጣቶች በእውቀታቸው ሥራ እንዲፈጥሩና ሀገር እንዲገነቡ አቅማቸውን እያሳደገ መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለፁ።
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሲካሔድ የቆየው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም ተጠናቋል።

በመድረኩ የተገኙት አቶ አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገሮች በልማት በሚተሳሰሩባቸው ምቹ ሁኔታዎች ላይ በትኩረት እየሰራች ነው።
ከእነዚህም ውስጥ የአህጉሪቱ ወጣቶች በልማት፣ በኢኮኖሚና በስራ እድል ፈጠራ የሚቀናጁበትን ሁኔታ ማመቻቸት አንዱና ዋነኛው መሆኑን አስረድተዋል።
ይህም እምቅ የተፈጥሮ ሀብትን በማልማት ጥቅም ላይ ለማዋል ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ በለውጡ ዓመታት ብዝሃ ኢኮኖሚ እና አካታች ልማትን ከክህሎት መር የሥራ ፈጠራ፣ የትምህርትና የስልጠና ፖሊሲ ጋር በማስተሳሰር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበችበት ነው ብለዋል።
በተለይም በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በማዕድን ልማት፣ በቱሪዝምና በዲጂታል ኢኮኖሚ ተከታታይ ፈጣን እድገትና በርካታ የሥራ ዕድል እየተፈጠረ መሆኑን አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ ለክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የሰው ሀብት ልማት የሰጠችው ትኩረት በእውቀታቸው ሥራ የሚፈጥሩ እና ሀገርን የሚገነቡ ወጣቶችን ማፍራት እያስቻለ ነው ብለዋል።
የአህጉሪቱን ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ አካታች የኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው በዚህ ረገድ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ሀገራት በትብብር መስራት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ወጣቶች ሥራ ፈጣሪና የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል።
አማራጭ የሥራ እድሎችን የማስፋት፣ በየዘርፉ የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን የማስረፅና ወጣቱ በኢኮኖሚው ላይ ያለውን ተሳትፎ ማጉላት ላይ ትኩረት መደረጉን አብራርተዋል።
የአፍሪካ ሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም የአህጉሪቱ ወጣቶችና ሥራ ፈጣሪዎች ያላቸውን ትስስር እንዲያጠናክሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አስታውቀዋል።
ፎረሙ የአፍሪካ ሀገራት በቀጣይ በዘርፉ በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ስምምነት ከማድረግ ባለፈ ቀጣይ በንግድና ሥራ ፈጠራ ላይ አበክረው ለመስራት አቅጣጫዎችን ያስቀመጡበት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026