የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ የመስኖ አውታሮችን በማስፋፋት የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል - ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር ኢ/ር)

Jul 8, 2025

IDOPRESS

ሸካ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመስኖ አውታሮችን በማስፋፋት የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በሸካ ዞን በየኪ ወረዳ ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክት መርቀዋል።

በወረዳው አላሞ ቀበሌ የተገነባው ቡቢ አነስተኛ የመስኖ አውታር ከ66 ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ800 በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል።

የክልሉ መንግስት የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የመስኖ አውታሮችን ማስፋፋት ላይ አተኩሮ እየሰራ ነው ብለዋል።


ይህም ክልሉ ያለውን የግብርና አቅም አሟጦ ለመጠቀምና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ጉልህ ሚና እንዳለው ጠቅሰዋል።

ባለፉት አራት ዓመታት 22 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተገንብተው የእርሻ ሥራን ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በዚህም ከ1 ሺህ 400 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ማልማት እንደተቻለ ተናግረዋል።

በቀጣይም የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታን በማጠናከር የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሠራል ብለዋል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የክልሉና የዞን እንዲሁም የወረዳ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.