
ሸካ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመስኖ አውታሮችን በማስፋፋት የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በሸካ ዞን በየኪ ወረዳ ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክት መርቀዋል።
በወረዳው አላሞ ቀበሌ የተገነባው ቡቢ አነስተኛ የመስኖ አውታር ከ66 ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ800 በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ታውቋል።
የክልሉ መንግስት የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የመስኖ አውታሮችን ማስፋፋት ላይ አተኩሮ እየሰራ ነው ብለዋል።

ይህም ክልሉ ያለውን የግብርና አቅም አሟጦ ለመጠቀምና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ጉልህ ሚና እንዳለው ጠቅሰዋል።
ባለፉት አራት ዓመታት 22 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተገንብተው የእርሻ ሥራን ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በዚህም ከ1 ሺህ 400 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ማልማት እንደተቻለ ተናግረዋል።
በቀጣይም የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታን በማጠናከር የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሠራል ብለዋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የክልሉና የዞን እንዲሁም የወረዳ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026