
አዳማ፤ ሰኔ 25/2017 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ህብረተሰቡን እና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የከተሞችን እድገት ለማፋጠን በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መገኘቱን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ አስታወቁ።
ሚኒስቴሩ የ2017 በጀት አመት የስራ አፈፃፀምና የ2018 ዕቅድ ከባለድርሻ አካላት ጋር በአዳማ እየገመገመ ነው።

መድረኩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፣ የአገሪቱ ከተሞች ባለፉት ጥቂት ዓመታት እያደጉና ለህብረተሰቡ የሚያስገኙት ጥቅም ከፍ እያለ መጥቷል።
በበጀት ዓመቱ የከተሞችን እድገት ለማፋጠንና ለህብረተሰቡ የሚሰጡ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ስራዎችን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል።
በተለይም በበጀት ዓመቱ የከተሞችን እድገት ለማፋጠን ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰው በዚህም የከተሞች ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን ቀልጣፋ በማድረግ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለማስወገድ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በመኖሪያ ቤቶች ግንባታ፣ በከተማ ግብርና፣ በከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት እንዲሁም በካዳስተር ትግበራ ውጤታማ ስራ መከናወኑን አስረድተዋል።
ከተሞችን ለኑሮ ምቹና ሳቢ ከማድረግ ባለፈ የከተሞችን ገቢ ለማሳደግ የማዘጋጃ ቤት አገልግሎትን ለማዘመን፣ የከተሞች መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት ረገድ በርካታ ውጤቶች መገኘታቸውንም አስረድተዋል።
የከተሞች የምግብ ዋስትና መርሃ ግብርም የበርካታ ዜጎችን ህይወት በመቀየር የሥራና የቁጠባ ባህልን ማጎልበት መቻሉን ሚኒስትሯ ተናግረዋል።
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር አማካሪ አቶ ተስፋዬ ሀይለሚካኤል በመድረኩ ላይ ባቀረቡት ሪፖርት እንዳመለከቱት በከተሞች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል በከተማ በምግብ ዋስትና መርሃ ግብር 15 ቢሊዮን ብር ስራ ላይ መዋሉን አመልክተዋል።

በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን በተሰማሩበት የምግብ ዋስትና መርሃ ግብር ከእለት ገቢያቸው 770 ሚሊዮን ብር በመቆጠብ ወደ ሌላ የልማት ስራ መሸጋገራቸውን ጠቁመዋል።
የማዘጋጃቤታዊ ገቢ ለማሳደግ በተደረገ ጥረት 76 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ገልጸው አፈፃፀሙ ከአምና ጋር ሲነፃፀር በ30 ቢሊዮን ብር ብልጫ ማሳየቱን አብራርተዋል።
በከተሞች ማዘጋጃቤታዊ አገልግሎት የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ፣ የአረንጓዴ ልማትና በመንገድ መሰረተ ልማት አቅርቦት ላይ መሻሻል መታየቱን ጠቅሰዋል።
በመድረኩ ላይ የሚኒስቴሩ ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ነው።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026