
ቦንጋ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሻይ ልማትን በማስፋፋት ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በቦንጋ ከተማ አስተዳደር የሚገኘውን የዲንቻ የሻይ ችግኝ ጣቢያ ተመልክተዋል።
የሻይ ልማት ችግኝ ጣቢያው በክልሉ የሻይ ልማትን ለማስፋፋት የሻይ ችግኝ ከሚዘጋጅባቸው ጣቢያዎች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው።
በምልከታው ርዕሰ መስተዳድሩ ችግኞችን በአግባቡ አፍልቶ ተደራሽ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት የሚበረታቱና መጠናከር ያለባቸው መሆኑን ገልጸው፣ አርሶ አደሩ በሻይ ልማት በስፋት ተሰማርቶ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆን የክልሉ መንግስት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ሀላፊ ማስረሻ በላቸው በክልሉ የሻይ ልማትን ለማስፋት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በልማቱ የአርሶ አደሩን የልማት ተሳትፎ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው፣ ባለሀብቶችን በመጋበዝ ፋብሪካ እንዲያቋቁሙ ለማድረግም እንቅስቃሴ መጀመሩን ተናግረዋል።
የካፋ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ ልማት መምሪያ ሀላፊ ጋዎ አባመጫ በበኩላቸው፣ በፕሮጀክትና በተደራጁ አርሶ አደሮች ብቻ ለበርካታ ዓመታት ተወስኖ የቆየውን የሻይ ልማት ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም በአራት ወረዳዎች የችግኝ ጣቢያዎችን በማቋቋምና ለቀጣይ ዓመት ተከላ የሚሆን ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለማዘጋጀት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
ከዚህ ቀደም የሻይ ልማት ከሚካከናወንባቸው 7 ቀበሌዎች በተጨማሪ 22 ቀበሌዎች ላይ ልማቱን ለማስፋት የሚሳተፉ አርሶ አደሮችና የመሬት ልየታ ሥራ ትኩረት ተሰጥቶ እየተከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል።

ይህም ከዚህ ቀደም በአንድ አካባቢ ብቻ ተወስኖ የቆየውን ልማት ለማስፋትና በዘርፉ የሚሰማሩ የአርሶ አደር ማህበራትን ቁጥር ለማሳደግ ይረዳል ብለዋል።
በተጨማሪም ወደ ዩኒየን ደረጃ በማሳደግ የገበያ ችግርን ለመፍታትና እሴት ጨምሮ ምርቱን ለገበያ ለማቅረብ ዕድል ይፈጥራል ነው ያሉት።
በዲንቻ የሻይ ልማት ችግኝ ጣቢያ ጉብኝት ላይ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026