
ሀዋሳ ፤ሰኔ 24/2017 (ኢዜአ) ፡-በዲጅታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ በእውቀትና ክህሎት የዳበሩ ባለሙያዎችን በማፍራት በተቋማት የአገልግሎት አሰጣጡን የማሻሻል ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የሲዳማ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የሲዳማ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ በክልሉ ለዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስን የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አሰፋ ጉራቻ፤ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና የተገልጋዮችን ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችሉ አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን አንስተው ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በተደረገ የዳሰሳ ጥናት የተገልጋዮች እርካታ ከ47 በመቶ ወደ 66 ነጥብ 3 በመቶ ከፍ ማለቱ ተመላክቷል።
ለመሻሻሉ ምክንያት የማዘጋጃ ቤቶች፣ ትራንስፖርት፣ የገቢዎችን ጨምሮ 7 የተለያዩ ሴክተሮችን የአገልግሎት ክፍተቶች በመለየት በቴክኖሎጂ ጭምር የታገዘ አሰራር በመዘርጋት መሆኑን አስረድተዋል።
በቀጣይም አገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ለማጠናከር በድጅታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር በመዘርጋት በእውቀትና በክህሎት የዳበረ አገልጋይ የመፍጠር ትኩረት ይደረጋል ሲሉ አረጋግጠዋል።
ለተመደቡበት የሥራ ዘርፍ ቃላቸውን ጠብቀውና ሃላፊነት ወስደው የማገልገል ችግር ያለባቸው አመራርና ሰራተኞች ሲያጋጥሙ በአሰራሩ መሰረት እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም ተናግረዋል።

የሲዳማ ክልል ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ዳይሬክተር ወይዘሮ ታደለች ዮሐንስ፤ በቢሮው እየተደረጉ ያሉ የአሰራር ማሻሻያዎች እንዲሁም የድጋፍና ክትትል ስራዎች ለውጥ ማምጣታቸውን አንስተዋል።
በዚህም የአገልጋዮች አቅም እየዳበረ የተገልጋዮች እርካታም እየተሻሻለ መምጣቱን ተናግረዋል።፡
በሥልጠናው ከ240 በላይ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026