
አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦በፌደራል የመንግሥት መስሪያ ቤቶች 32 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ያልተሰበሰበ ሂሳብ መኖሩን የፌደራል ዋና ኦዲተር መሰረት ዳምጤ ተናገሩ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው 39ኛ መደበኛ ስብሰባው የፌዴራል ዋና ኦዲተር የፌዴራል መንግሥት መስሪያ ቤቶች የ2016 በጀት ዓመት ሒሳብ የፋይናንሺያል፣ የሕጋዊነት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርትን አዳምጧል።
የፌደራል ዋና ኦዲተር መሰረት ዳምጤ ባለበጀት መስሪያ ቤቶች የመንግስትን ህግና መመሪያ ተከትለው በጀትን ስለመጠቀማቸው የተከናወነውን የኦዲት ሪፖርት ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

በፌደራል የመንግሥት የክፍያ መመሪያ መሰረት ለውሎ አበልና ለመጓጓዣ የተሰጠ ቅድሚያ ክፍያ ሰራተኛው ሥራውን አጠናቆ ከተመለሰ በኋላ በሰባት ቀናት ውስጥ መወራረድ እንዳለበት ያስቀምጣል።
በተመሳሳይ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በሒሳብ አያያዝ መመሪያ መሰረት ደግሞ ለሥራ ማስኬጃ የተሰጠ ቅድሚያ ክፍያ በሰባት ቀናት ውስጥ መወራረድ እንዳለበት ያስቀምጣል፡፡
በዚህም በ137 መሥሪያ ቤቶችና በ20 የገቢዎችና ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ላይ የተሰብሳቢ ሂሳብ ደንብና መመሪያን ተከትለው መፈጸማቸውን ለማረጋገጥ ኦዲት መደረጉን አብራርተዋል።
በዚህም በአጠቃላይ 32 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በወቅቱ ያልተወራረደ ወይንም ያልተሰበሰበ ሂሳብ መኖሩ በኦዲት መረጋገጡን በሪፖርታቸው አመላክተዋል፡፡
ይህ ሂሳብ መወራረድ ከነበረበት ጊዜ ከአንድ ወር እስከ አስር አመት የቆየ መሆኑንም ዋና ኦዲተሯ አመላክተዋል።
በመሆኑም ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ በወቅቱ እንዲወራረድ አለማድረግ የመንግሥትን ገንዘብ የሚያባክን በመሆኑ በአስቸኳይ መወራረድ እንዳለበት ማሳሰቢያ መሰጠቱን ጠቁመዋል።
ለረጅም ዓመታት ሳይሰበሰቡ የተገኙ ሂሳቦች እንዲወራረዱ አስፈላጊው ክትትል እንዲደረግ፣ ሊሰበሰቡ የማይችሉትን በመንግሥት መመሪያ መሠረት ከመዝገብ እንዲሰረዙ ለተቋማቱ ማሳሰቢያ መላኩንም ገልጸዋል፡፡
በተመሳሳይ ያልተሰበሰበ ውዝፍ የገቢ ሂሳብ፣ ገቢ ያልተደረገ የጉዳት ካሳ፣ ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ የተመዘገቡና ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ ያልተቻለ ሂሳብና ሌሎች የኦዲት ሪፖርቶችን አቅርበዋል።
ደንብና መመሪያን ያልተከተለ የወጪ ሂሳብ፣ የግዥ አዋጅ ደንብና መመሪያን ያልተከተለ ግዥ መፈጸምና ሌሎች የኦዲት ግኝቶችም ቀርበዋል።
በመንግስት የግዥ አዋጅ ደንብና መመሪያ መሰረት ግዥ መፈጸማቸውን ለማረጋገጥ በ70 መስሪያ ቤቶችና በሰባት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች በተደረገ ኦዲት ከ 404 ሚሊዮን ብር በላይ መመሪያውን ያልተከተለ ግዥ መፈጸሙ ተረጋግጧል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026