የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የአፍሪካና አሜሪካ የግሉ ዘርፍ ትብብር ለጋራ ብልጽግና ወሳኝ ነው - አፍሪካ ኅብረት

Jun 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካና የአሜሪካ የግሉ ዘርፍ ትብብር ለጋራ ብልጽግና ወሳኝ መሆኑን የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሞሃመድ አሊ የሱፍ ተናገሩ።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከስፍራው እንደዘገበው ሊቀ-መንበሩ በአንጎላ እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ አሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር የአሜሪካና የአፍሪካ የንግድና የኢንቨስትመንት ትብበር መጠናከር አለበት ብለዋል።

በሁለቱ ወገን ያለው የቢዝነስ ትስስር የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል።

አፍሪካ አሁን ላይ ባላት ከፍተኛ የተፈጥሮና የሰው ሃብት እንዲሁም የፈጠራ ሥራ መስፋፋት ወሳኝ የለውጥ ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ ጠቁመው ይህንን ወደፊት ማስኬድ ይገባል ነው ያሉት።

አፍሪካ ኅብረት በአህጉሪቱ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ በተለያዩ ዘርፎች እንዲጎለብትና የአህጉሪቱ እድገት ቀጣይነት እንዲኖረው እየደገፈ መሆኑን ተናግረው ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ከዚህ አንጻር የአሜሪካ ኩባንያዎች በተለያዩ የአፍሪካ አገራት በኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ ጠይቀው፤ አሁን ላይ ከንግግር ባለፈ አጀንዳ 2063ን ለማሳካት የጋራ ጥረትና ተግባር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

በጉባኤው ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴን ጨምሮ የተለያዩ የአፍሪካ አገራት መሪዎች፣ሚኒስትሮች፣ የመንግሥታት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣የሁለቱም ወገን የቢዝነስ መሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026