
ወላይታ ሶዶ፤ ሰኔ 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመረጃዎችን ጥራትና ተዓማኒነት ለማሳደግ የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርዓትን ማጠናከር እንደሚገባ ተመላከተ።
በክልሉ የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርዓትን ለማሳደግ ያለመ መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በመድረኩ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ክላስተር አስተባባሪ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ተፈሪ አባተ ለሁለንተናዊ ዕድገት የመረጃ አያያዝን ማዘመን አስገዳጅ መሆኑን ተናግረዋል።

ለተግባራዊነቱም የክልሉ መንግስት መረጃን የመሰብሰብ፣ የመተንተን እና የማደራጀት ስራዎችን ለማዘመን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
መረጃን በአግባቡ ሰብስቦ ጥቅም ላይ በማዋል የህዝብን ፍትሃዊ ተጠቃሚነትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄን ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፍቃደ ስላሴ ቤዛ ናቸዉ።
የክልሉን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና መልክዓ ምድራዊ የልማት መረጃዎችን በጥራት በመሰብሰብ በአግባቡ ሰንዶ ለመያዝ ጥረት መደረጉንም አስረድተዋል።

የተሰበሰቡና የተተነተኑ መረጃዎች በዳታ ቤዝ ቋት ተደራጅተው ለማስቀመጥ የተሰሩ ተግባራትን ለማጠናክር መድረኩ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡
የመረጃዎችን ጥራትና ተዓማኒነት ለመጠበቅ የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርዓትና ቋት ማዘጋጀት አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ይህም መረጃ ለተመራማሪዎች፤ ለፖሊሲ አውጭዎችና ለውሳኔ ሰጭ አካላት ተደራሽ አንዲሆን በቴክኖሎጂ መደገፉን ተናግረዋል፡፡
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስነ-ህዝብ ልማት ፈንድ ፕሮግራም አስተባባሪ ወይዘሮ ገዙ ብርሃኑ በበኩላቸው ጥራቱን የጠበቀና ወቅታዊ መረጃን መሰብሰብ ለሀገር ዕድገት ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል ።
በዚህም ረገድ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የሀገር ውስጥ ስታቲስቲክስ መረጃዎችን በመሰብሰብ በማቀነባበር እና ተንትኖ ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ረገድ ከፕሮግራሙ ጋር በጋራ መስራቱን ተናግረዋል።

ፕሮግራሙ መረጃን በማመንጨትና ለተጠቃሚዎች ለማቅረብ ከሚደረጉ ጥረቶች አንፃር የህዝብና ቤት ቆጠራ፣ የስነ ህዝብ ጤና ጥናት እንዲሁም ሌሎችንም እንደሚደግፍ አመልክተዋል።
በመድረኩም የክልል፣ የዞን እና የከተማ አስተዳደሮች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026