
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2017(ኢዜአ)፦ በኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የተመራ ከፍተኛ ልዑክ የአፍሪካና የአሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ ላይ ለመታደም በአንጎላ ርዕሰ መዲና ሉዋንዳ ገብቷል።
በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የተመራው ልዑክ ሉዋንዳ ሲደርስ በሀገሪቱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
የዘንድሮውን የአፍሪካና የአሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር አሜሪካ አፍሪካን በተመለከተ የምትከተለው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ድጋፍን መሰረት ካደረገው ወደ ንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት ለመቀየር መወሰኑን ተከትሎ የሚካሄድ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

ዛሬን ጨምሮ ለአራት ቀናት በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ ሚኒስትሮች፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የሁለቱም ወገን የቢዝነስ መሪዎችን ጨምሮ 1ሺህ 500 ተሳታፊዎች በጉባኤው ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ጉባኤው በአፍሪካና በአሜሪካ መካከል ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር በሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎችና ዕድሎች ዙሪያ በመምከር ቀጣይ አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀምጥ ታምኖበታል።
በጉባኤው ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ንግግር የሚያደርጉ ሲሆን ጎን ለጎንም የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶች እንደሚያደርጉ ኢዜአ ለማወቅ ችሏል።
በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ልዑክ አባላት በጉባኤው በፓናል ውይይትና በሌሎች ቁልፍ ስብሰባዎች ላይ ተሳትፎ ያደርጋል።
ኢትዮጵያ በውጭ ግንኙነት ፖሊሲዋ በተለይም ለኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ በሰጠችው ትኩረት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመሳብ፣ የሁለትዮሽ የንግድ ትስስርን በማጠናከርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለኢትዮጵያ ምርቶች አዳዲስ ገበያዎችን በማፈላለግ በኩል አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል።
መሰል ጉባኤዎችም ኢትዮጵያ በዘርፉ እያስመዘገበች ያለውን ውጤት ይበልጥ ከማጠናከር በዘለለ ሀገሪቱ በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ያላትን እምቅ አቅም ለማስተዋወቅና ጥቅም ላይ እንዲውል እድል በመፍጠር ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው ይጠበቃል።
ይህም ኢትዮጵያ ገቢራዊ ያደረገችው የኢኮኖሚ ሪፎርም ተግባራዊነት በማቀላጠፍ የኢኮኖሚያዊ እድገቱን በማስቅጠል ትልቅ ሚና እንደሚኖረውም እንዲሁ።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026