
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ የባህር በር ለኢትዮጵያ የፖለቲካ አጀንዳ ሳይሆን የህልውናዋ ጉዳይ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የሁልጊዜም ፍላጎት ከጎረቤቶቿ ጋር በጋራ መልማት መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሰላም መሆንና መልማት ለቀጣናው ዕድገት በጎ ሚና እንደሚጫወትም ጨምረው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር እና ከፍተኛ የህዝብ ብዛት አላት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላም እና ልማት ለኢትዮጵያ ቁልፍ ጉዳዮች እንደሆኑ ጎረቤቶቿ ሊረዱ እንደሚገባ አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋ በህጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ እየሰራች እንደምትገኝም ተናግረዋል።
የባህር በር ጉዳይ የፖለቲካ አጀንዳ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዳዩ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ ነው ብለዋል።
የባህር በር አለመኖር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ እንደሚገኝ ገልጸው ጉዳዩ አፈጣኝ መፍትሄ እንደሚያሻው አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ የባህር በር እንደሚፈያስፈልጋት እና ይህም በንግድ ህጎች አማካኝነት ምላሽ ያገኛል ብለው እንደሚያምኑም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የጎረቤት ሀገራት የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ በቀናነት እንዲረዱትና ጥያቄው ከመልማት እና ከማደግ ካለ ጽኑ ፍላጎት የመነጨ እንደሆነ መገንዘብ እንደሚገባቸው አንስተዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026