
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ የስራ ባህልን በትውልድ ውስጥ ለማስረጽ የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ መገናኛ ብዙሃንን ጨምሮ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
"የስራ ባህል ምርታማነት ለሀገር ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሃሳብ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡

በውይይቱ ማጠቃለያ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እንዳሉት የስራ ባህል ግንባታ ስኬታማ እንዲሆን ትውልድን ከታች ጀምሮ መቅረጽ ይገባል፡፡
ትውልድን በመቅረጽ የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ መገናኛ ብዙሃንን ጨምሮ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ለሙያ ያለን አመለካከት የአስተሳሰብ ለውጥ የሚፈልግ ነው ያሉት ሚኒስትሯ ከቤተሰብ ጀምሮ የስራ ባህልን ማዳበር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል፡፡
ያሉንን አቅምና ጸጋ መለየት በዛ ላይ ተመስርቶ ፈጠራና ፍጥነትን በማከል ውጤታማ ስራ ማከናወን ይጠበቅብናል ነው ያሉት፡፡
በዚህ ረገድ እንደሀገር መልካም ጅምሮች በመኖራቸው ይህንኑ በማስፋት ለውጤት እንዲበቃ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡
ምርታማነትን ማሳደግ በሚያስችሉ የቴክኖሎጂና የሰው ሃይል ልማት ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ ተነስቷል፡፡
እንደ ኮሪደር ልማትና ህዳሴ ግድብ ያሉ መልካም ተሞክሮዎችን ማስፋት እንደሚገባም ነው የተገለጸው፡፡
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026