
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017 (ኢዜአ)፦ በበጀት አመቱ 11 ወራት ከ7 ነጥብ 21 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ከወጪ ንግድ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 38ኛ መደበኛ ስብሰባ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የ11 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ተወያይቷል።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንደተናገሩት በበጀት አመቱ በሀገሪቱ የወጪ ንግድ ታሪክ ከፍተኛ የሆነ ገቢ ተገኝቷል።
ከጠቅላላ የወጪ ንግድ 4 ነጥብ 59 ቢሊየን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰው በአፈጻጸም ከእቅድ በላይ 7 ነጥብ 21 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።
በበጀት አመቱ መጨረሻ ከ 8 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።
በበጀት አመቱ 11 ወራት ከወጪ ንግድ የተገኘው ገቢ ከ2016 በጀት አመት ጋር ሲነጻጸር ከ 3 ነጥብ 96 ቢሊየን ዶላር በላይ ጭማሪ ማሳየቱንም ጠቅሰዋል።

በማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ከተሳኩ ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች መካከል የወጪ ንግድ ዘርፍ ከፍተኛ አፈጻጸም እየተመዘገበበት መሆኑንም አክለዋል።
በወጪ ንግድ ምቹ ምህዳር መፈጠሩ፣ የተለያዩ የህግና አሰራር ማነቆዎች መፈታታቸው፣ ከላኪዎች እና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በተሻለ ቅንጅት በመሰራቱ በአገሪቱ ታሪክ ከፍተኛውን ገቢ ማግኘት ተችሏል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026