የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የጅግጅጋ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ውበትና ድምቀት እያጎናጸፋት ነው

Jun 20, 2025

IDOPRESS

ጅግጅጋ ፤ሰኔ 12/2017 (ኢዜአ) የጅግጅጋ የኮሪደር ልማት ከተማዋን ውበትና ድምቀት እያጎናጸፋት መሆኑን ነዋሪዎች ገለጹ።

የጅግጅጋ ከተማ ኮሪደር የመጀመሪያ ምዕራፍ ልማት 10 ኪሎ ሜትር መንገዶች በ6 ሳይቶች ላይ እየተከናወነ ነው ።

የኮሪደር ልማቱን አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች የኮሪደር ልማቱ የከተማውን ገጽታ እንደሚጨምር ተናግረዋል።


ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል መምህር ሙሳ ሃጂ፤ ኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ለስራና ለኑሮ ምቹ ከማድረጉ ባለፈ ለአካል ጉዳተኞች ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ የነበረን ሁኔታ መቀየሩን አስረድተዋል።


ሌላው የከተማው ነዋሪ አቶ ፋራህ ዑመር በበኩላቸው ኮሪደሩ ጠባብና ለእንቅስቃሴ አስቸጋሪ የነበረን የከተማዋን መንገድ በማስፋት ከተሽከርካሪዎች አደጋ ራስን ለመጠበቅ ምቹ አጋጣሚ የፈጠረ ነው ብለዋል።

የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ፣ ለአካባቢያቸው እድገትም ትልቅ እድል መሆኑንና ከተማዋን ውበትና ድምቀት እያጎናጸፋት መሆኑን ገልጸዋል።


የኮሪደር ልማቱ የእግረኞች፣ የተሽከርካሪዎች እና የሳይክል መንገዶች ማካተቱ የከተማዋን የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንደሚያሳልጠው የገለጹት ደግሞ ሌላኛው የከተማ ነዋሪ አቶ አብራሃም ተፈሪ ናቸው ።

ይህንን ተሞክሮም ወደ ሌሎች የክልሉ ከተሞች ማስፋት እንደሚገባም አመልክተዋል።


የጅግጅጋ ከተማ ከንቲባ ኢንጅነር ሻፊ መአልን፤ የኮሪደር ልማቱ የከተማዋ ነዋሪዎች የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የነበረውን የመሰረተ ልማት ተደራሽነት እየፈታ መሆኑን አንስተዋል።

የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን የ30 አመታት የእድገት ዲዛይን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ጠቁመው ይህን ለማሳካት ከነዋሪዎች ጋር በመወያየት ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል።


በኮሪደር ልማቱ የተካተቱት 10 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ ስድስት የአስፋልት መንገዶች ግንባታም 85 በመቶ መድረሱን ተናግረው የመንገዶቹ ግንባታ ቀደም ሲል ይደርስ የነበረን የጎርፍ አደጋን እንደሚያስቀርም ጠቁመዋል።

በኮሪደር ልማቱ 5 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ፓርክ፣ የህጻናት መጫወቻ ቦታዎች፣ የመዝናኛ ሥፍራዎች እና ካፍቴሪያዎች መካተታቸውን አክለዋል።

የኮሪደር ልማቱ እስካሁን በተጠናቀቀባቸው አካባቢዎች የተሽከርካሪዎችና የእግረኞች መንገድ እንዲሰፋ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰው ለረጅም ጊዜ የሚያገለግሉ መሠረተ ልማቶችን በማስተሳሰር በመሬት ስር እንዲሄዱ መደረጉንም ጠቁመዋል።

ከዚህ ባለፈም ልማቱ በከተማው ለ12 ሺህ 500 ዜጎች የሥራ እድል እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026