የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የሳይበር ጥቃቶችን ለመቋቋም የሳይበር ደህንነት ላይ የሚሰሩ ምርምሮችን መደገፍ ያስፈልጋል - ሚኒስቴሩ

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 6/2017(ኢዜአ)፦ በየጊዜው የሚቀያየረውን የሳይበር ጥቃት ለመቋቋም የሳይበር ደህንነት ላይ የሚሰሩ ምርምሮችን መደገፍ እንደሚያስፈልግ የኢኖቬሸንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ።

የኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት ማህበር በሳይበር ደህንነት ላይ ትኩረት ያደረገ “ዓለም አቀፍ የሳይበር ደህንነት እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በኢትዮጵያ" በሚል ሀሳብ ጉባዔ እያካሄደ ይገኛል።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ፎዚያ አሚን(ዶ/ር) በጉባዔው መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት፤ የሳይበር ደህንነትን ለማስጠበቅ የፈጠራ ስራዎች ወሳኝ ናቸው።

ይህንንም ውጤታማ ለማድረግ የሳይበር ደህንነት ላይ የሚከናወኑ ምርምሮችን መደገፍ አስፈላጊ ነው ብለዋል።

የሳይበር ደህንነት መሪ በሚሆነው ትውልድ ላይ መስራት እንደሚገባ ገልጸው፤ የሳይበር ደህንነት ላይ የሚሰሩ ምርምሮችን በማጠናከርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተደራሽ በማድረግ በዘርፉ አዎንታዊ ሚና መጫወት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

ከምሁራን፣ ከሲቪክ ማህበራትና ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በትብብር መስራት እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።

የሳይበር ደህንነት የማስጠበቅ ስራን ስኬታማ ለማድረግ ትብብር ወሳኝ መሆኑን አመላክተው፤ በዘርፉ ያለውን እውቀት፣ መልካም ተሞክሮና ሀብት በመጠቀም በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።

የሳይበር ደህንነት ተግዳሮቶችን ለማስወገድና የጋራ መፍትሄዎችን ለመፍጠር ከአጋር አካላት ጋር የሚሰሩ ስራዎችን እንደሚጠናከሩም ተናግረዋል።

ጉባዔው የዲጂታል ዘርፉን ቀጣይ ምዕራፍ የሚያመላክት እና የዲጂታል ሽግግሩን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ግብዓት ለመሰብሰብ ያግዛል ነው ያሉት።


የዓለም አቀፍ የቴሌኮሙኒኬሽን ሕብረት የአፍሪካ ቀጣናዊ ዳይሬክተር ኢማኑኤል ማናሳህ እንዳሉት የዲጂታል ሽግግር ስራዎችን ለማጠናከር ትስስር መፍጠር፣ የዲጂታል ክህሎትና የፈጠራ ችሎታን ማዳበር ያስፈልጋል።

የሳይበር ደህንነትን ማስጠበቅ፣ መዋዕለ ነዋይን ማፍሰስ፣ ህግና ፖሊሲዎችን ማሻሻል እንዲሁም ምቹ ከባቢ መፍጠር ወሳኝ መሆኑን አክለዋል።

አፍሪካውያን በትብብር በመስራት ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ተመጣጣኝና ቀልጣፋ የዲጂታል አገልግሎት እንዲጠናከር ማድረግ አለባቸው ብለዋል።


የኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት ማህበር ፕሬዝዳንት ብርሃኑ በየነ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የሳይበር ደህንነት ስጋቶች ውስብስብና በየጊዜው ተለዋዋጭ በመሆናቸው አፍሪካውያን በጋራ መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል።

ይህም ዲጂታል እሴቶችን እና መሰረተ ልማቶችን መጠበቅ እንደሚያስችል ተናግረዋል።

ኮንፍረንሱ በሀገር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ አካላት፣ ተመራማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የሀሳብና የልምድ ልውውጥ ለማድረግና በጋራ እንዲሰሩ እድል ይፈጥራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026