
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፡- የኦዲት ባለድርሻ አካላት ፎረም የተቋማትን አሰራር በመፈተሽ የቁጥጥር ስርዓትን ለማጠናከርና ተጠያቂነትን ለማስፈን አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ።
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኦዲት ባለድርሻ አካላት ፎረም የ2017 በጀት አመት አፈፃፀም ላይ ውይይት አካሒዷል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር) የኦዲት ባለድርሻ አካላት ፎረም እቅድ አፈጻጸም ማጠቃለያ ሪፖርት አቅርበዋል።
ቋሚ ኮሚቴው የፌዴራል ተቋማት በመንግስት የተመደበ በጀት አጠቃቀማቸውን፣ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎች፣ ህጎች፣ የአሰራር ስርዓቶችንና እቅዶችን መፈተሽ ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ፎረሙ አስፈጻሚ ተቋማትና ሌሎች ቋሚ ኮሚቴዎች ለኦዲት ሪፖርት የሚሰጡት ትኩረት እንዲጨምር እድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ ከኦዲት ግኝት ጋር ተያይዞ አስተያየት ከተሰጣቸው ተቋማት ውስጥ ለሶስት ተቋማት የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲሁም ለኃላፊዎች የገንዘብ ቅጣት እንዲጣልባቸው ማድረግ መቻሉን ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ ለሰባት የመንግስት ተቋማት የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲደርሳቸው ተደርጓል ብለዋል።
በበጀት ዓመቱ በተከናወኑ የኦዲት ግኝት ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት መቻሉንም ተናግረዋል።
ይህም የኦዲት ባለድርሻ አካላት ፎረም የተቋማትን አሰራር በመፈተሽ የቁጥጥር ስረዓትን ለማጠናከርና ተጠያቂነትን ለማስፈን አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል።
በውይይቱ ላይ የተለያዩ የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026