የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ክልሉ የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም በጥናት ላይ የተመሰረተ ስራ ተከናውኗል - ቢሮው

Jun 12, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፦ የሲዳማ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን አቅም መጠቀም የሚያስችል ስራ እያከናወነ መሆኑን የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በዘርፉ ላይ ባስጠናቸው የተለያዩ ጥናቶች ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።

የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጎሳዬ ጎዳና በዚህ ጊዜ እንደገለጹት ቢሮው በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን አቅም መጠቀም የሚያስችል በጥናት የተደገፈ ስራ እያከናወነ ነው።


ለዚህም ከ2014 ጀምሮ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የአምራች ኢንዱስትሪ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።

ፍኖተ ካርታውን ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል የ10 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድና ይህን ተግባራዊ ለማድረግ አቅሞችን ለይቶ የሚሳይ ጥናት መደረጉን አስረድተዋል።

የዛሬው መድረክም ባለድርሻ አካላት ለጥናቶቹ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችን እንዲያነሱ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

የጥናቱ ዋና ዓላማም አምራች ኢንዱስትሪው በስራ እድል ፈጠራ፣ ተኪ ምርቶችን በማምረት፣ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በሌሎች ወሳኝ ዘርፎች የሚያስገኘውን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ማሳደግ መሆኑንም አመልክተዋል።

በተለይም እንደክልል ያለውን ጠባብ መሬት በተገቢው በመጠቀም ወደ ኢንዱስትሪ ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞን ጨምሮ የክልል ቢሮ ኃላፊዎች የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ችሮታው አየለ(ዶ/ር) እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026