
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ ከተማ የተገነቡ የምርት ግብይት ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነቱን እና የዋጋ ንረትን በመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) የላፍቶ ቁጥር ሁለት ሁለገብ የገበያ ማዕከል ዛሬ መርቀው ስራ አስጀምረዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡ የገበያ ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን እንደ ድልድይ በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነቱን እና የዋጋ ንረትን በመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም ዛሬ የተመረቀው የላፍቶ ቁጥር 2 የገበያ ማዕከልም አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነቱን እና የዋጋ ንረትን በመቀነስ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
እስካሁን በከተማው በርካታ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ህብረተሰቡ ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝና የኑሮ ውድነቱን ለመቀነስ የገበያ መሰረተ ልማቶችን የማስፋት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የላፍቶ ቁጥር ሁለት ሁለገብ የገበያ ማዕከል በ8 ነጥብ 8 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባ ነው።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026