የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ለተረጋጋ የኢኮኖሚ ሥርዓት ግንባታ የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና ወሳኝ ነው-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

Jun 5, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፤ግንቦት 27/2017 (ኢዜአ)፡-ለተረጋጋ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት ግንባታ የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና ወሳኝ ነው ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ተናገሩ።

"የብልጽግና ጉዟችንና የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ ክልላዊ የንግዱ ማኅበረሰብ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።


በመድረኩ ላይ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንዳሉት፥ ለተረጋጋ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት ግንባታ የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና ወሳኝ ነው።

በተለይ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብ ኢንቨስትመንት፣ ኢንዱስትሪ፣የሥራ ዕድል ፈጠራና ማኅበራዊ አገልግሎትን ማጠናር እንደሚገባ ገልጸው፣ለዚህም የንግዱ ማህበረሰብ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

መንግስት የንግዱን ሥርዓት ለማሳለጥና ነጋዴውን ለማበረታታት የተለያዩ ማዕቀፎችን መተግበሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ኢንጂነር ነጋሽ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

የንግዱ ማህበረሰብም ይህን ዕድል በመጠቀም ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብና የተረጋጋ የገበያ ሥርዓት እንዲኖር ሚናውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።

መንግስት ጤናማ የንግድ ሥርአትን በመፍጠር ገበያን ለማረጋጋት የሚያደርገውን ጥረት ማገዝ እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የንግድ ሥራና የልማት እንቅስቃሴዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026