
ቦንጋ፤ግንቦት 27/2017 (ኢዜአ)፡-ለተረጋጋ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት ግንባታ የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና ወሳኝ ነው ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ተናገሩ።
"የብልጽግና ጉዟችንና የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ ክልላዊ የንግዱ ማኅበረሰብ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ላይ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንዳሉት፥ ለተረጋጋ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት ግንባታ የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና ወሳኝ ነው።
በተለይ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብ ኢንቨስትመንት፣ ኢንዱስትሪ፣የሥራ ዕድል ፈጠራና ማኅበራዊ አገልግሎትን ማጠናር እንደሚገባ ገልጸው፣ለዚህም የንግዱ ማህበረሰብ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
መንግስት የንግዱን ሥርዓት ለማሳለጥና ነጋዴውን ለማበረታታት የተለያዩ ማዕቀፎችን መተግበሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ኢንጂነር ነጋሽ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
የንግዱ ማህበረሰብም ይህን ዕድል በመጠቀም ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብና የተረጋጋ የገበያ ሥርዓት እንዲኖር ሚናውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።
መንግስት ጤናማ የንግድ ሥርአትን በመፍጠር ገበያን ለማረጋጋት የሚያደርገውን ጥረት ማገዝ እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የንግድ ሥራና የልማት እንቅስቃሴዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026