
ሠመራ፣ግንቦት 26/2017(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል የግብርና ግብዓት አጠቃቀም ላይ የታየው መሻሻል መጠናከር እንዳለበት ተመላከተ።
ግብርና ሚኒስቴር በአፋር ክልል የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት፣ አጠቃቀምና ስርጭት ላይ ከክልሉ ባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ መክሯል።
በመድረኩ የተገኙት በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ግብዓት አቅርቦት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ መንግስቱ ተስፋ እንዳሉት፥ መንግስት የተለያዩ የግብርና ግብዓቶችን በማቅረብ ምርታማነትን ለማሳደግ እየሠራ ነው።
በዚህም በአፋር ክልል በ2016 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እንዲጀመር ማስቻሉን ገልጸው፤ አፈፃፀሙም የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ የግብርና ግብዓት አጠቃቀም መሻሻል እየታየ መሆኑን አንስተው፥ ተግባሩ ሊጠናከር እንደሚገባም አመልክተዋል።
መድረኩ የተዘጋጀውም በክልሉ የተሳለጠ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና የግብርና ግብዓት አጠቃቀምን በተመለከተ ለባለድርሻ አካላት ግንዛቤ ለመፍጠር መሆኑንም ጠቁመዋል።
የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሐሩን ዓሊ በበኩላቸው፥ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት በቅርቡ የተጀመረ ቢሆንም በግብዓትነት መጠቀም ላይ ተስፋ ሰጪ አተገባበር ታይቷል ብለዋል።
በበጀት ዓመቱ በክልሉ በሚገኙ ሰባት ወረዳዎች የአፈር ማዳበሪያ በማቅረብ ላይ እንደሚገኙ የገለፁት ደግሞ በክልሉ የደንከሊያ ግብርና ግብዓት አቅርቦት ህብረት ስራ ዩኒየን ስራ አስኪያጅ አቶ መሰለ ይማም ናቸው።
ለአራት መሠረታዊ ማህበራትና ለኢንቨስተሮች ዩሪያና ዳፕ ማዳበሪያዎችን በማቅረብ ላይ መሆናቸውን ገልፀው፥ እስካሁን 25 ሺህ 995 ኩንታል ማዳበሪያ ማከፋፈላቸውን ገልፀዋል።
የጋሊ ኮማ ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን ስራ አስኪያጅ ወጣት ሰኢድ ሲራጅ በበኩሉ፥ 1 ሺህ 4 ኩንታል ማዳበሪያ ስርጭት ማከናወኑን ተናግሯል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026