የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ በበልግ ዝናብና በመስኖ ከለማው ሰብል ከ18 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል

Jun 3, 2025

IDOPRESS

ደቡብ ቤንች፤ግንቦት 24/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በበልግ ዝናብና በመስኖ ከለማው የአትክልትና ስራስር ሰብሎች ከ18 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።


የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸውን ጨምሮ ሌሎች የስራ ኃላፊዎች በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የሽንኩርት ማሳ ተመልክተዋል።


አቶ ማስረሻ በላቸው በወቅቱ እንዳሉት፥ በክልሉ በበልግ ዝናብና በሁለተኛ ዙር መስኖ ከ100 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ የለማው የአትክልትና ስራስር ሰብል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል።


ከለማው ማሳም ከ7 ሺህ ሄክታር በላዩ በሽንኩርት የተሸፈነ መሆኑን ተናግረዋል።


በአጠቃላይ በአትክልትና ስራስር ሰብል ከለማው ማሳ 18 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።


በተለይም በደቡብ ቤንች ወረዳ በአርሶ አደር ጓሮ የተጀመረው የሽንኩርት ልማት አሁን ላይ ተስፋፍቶ በኩታ ገጠም መመረት መቻሉ ከአካባቢው አልፎ ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል።


የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን በበኩላቸው፥በዞኑ እየተከናወኑ ባሉ የግብርና ስራዎች ውጤት እየታየ ነው ብለዋል።


በደቡብ ቤንች ወረዳ የተጀመረውን የኩታ ገጠም ሽንኩርት ልማት በዞኑ ውስጥ ባሉ ሁሉም ወረዳዎች እንዲስፋፋ ጥረት እንደሚደረግ አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026